የጎንደር ዩኒቨርሲቲ እና የሩሲያው የኢኮኖሚክስ ከፍተኛ ትምህርት ዩኒቨርስቲ የአፍሪካ ጥናት ማዕከል በትብብር በሚሰሩበት መንገድ ዙሪያ ተወያዩ

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ እና የሩሲያው የኢኮኖሚክስ ከፍተኛ ትምህርት ዩኒቨርስቲ የአፍሪካ ጥናት ማዕከል በትብብር በሚሰሩበት መንገድ ዙሪያ ተወያዩ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ እና የሩሲያው ኤችኤስኢ ዩኒቨርሲቲ የአፍሪካ ጥናት ማዕከል በትብብር ሊሰሩ የሚችሉባቸውን መስኮች በመለየት ውጤታማ ውይይት አድርገዋል። በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ካሳሁን ተገኝ የተመራው ስብሰባ፤ የጋራ ጥቅሞችን እና የአጋርነት እድሎችን በመፈለግ ላይ ያተኮረ እንደነበር የጎንደር ዩንቨርስቲ አስታውቋል። በኤችኤስኢ ዩኒቨርሲቲ የኢ-አስተዳደር ማጋራት ፕሮግራም ምክትል አስተባባሪ ፊሊፕ ግሪኒን፤ በምግብ ዋስትና፣ በግብርና ዘርፍ ዲጂታላይዜሽን፣ የልምድ ልውውጥ እና የጋራ ህትመቶችን በመሳሰሉ ቁልፍ ዘርፎች ላይ በትብብር እንደሚሰሩ ተናግረዋል። እነዚህ ዘርፎች የቴክኖሎጂ ፈጠራን ለማበረታታት ለተነደፉ የጋራ የምርምር ፕሮጀክቶች፣ የግራንት እድሎች እና ትምህርታዊ ፕሮግራሞች መሰረት ይሆናሉ ተብሏል።ምስሉ ከጎንደር ዩንቨርስቲ የማሕበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘ ነው። መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
Sputnik
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ እና የሩሲያው የኢኮኖሚክስ ከፍተኛ ትምህርት ዩኒቨርስቲ የአፍሪካ ጥናት ማዕከል በትብብር በሚሰሩበት መንገድ ዙሪያ ተወያዩ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ እና የሩሲያው ኤችኤስኢ ዩኒቨርሲቲ የአፍሪካ ጥናት ማዕከል በትብብር ሊሰሩ የሚችሉባቸውን መስኮች በመለየት ውጤታማ ውይይት አድርገዋል። በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ካሳሁን ተገኝ የተመራው ስብሰባ፤ የጋራ ጥቅሞችን እና የአጋርነት እድሎችን በመፈለግ ላይ ያተኮረ እንደነበር የጎንደር ዩንቨርስቲ አስታውቋል። በኤችኤስኢ ዩኒቨርሲቲ የኢ-አስተዳደር ማጋራት ፕሮግራም ምክትል አስተባባሪ ፊሊፕ ግሪኒን፤ በምግብ ዋስትና፣ በግብርና ዘርፍ ዲጂታላይዜሽን፣ የልምድ ልውውጥ እና የጋራ ህትመቶችን በመሳሰሉ ቁልፍ ዘርፎች ላይ በትብብር እንደሚሰሩ ተናግረዋል። እነዚህ ዘርፎች የቴክኖሎጂ ፈጠራን ለማበረታታት ለተነደፉ የጋራ የምርምር ፕሮጀክቶች፣ የግራንት እድሎች እና ትምህርታዊ ፕሮግራሞች መሰረት ይሆናሉ ተብሏል።ምስሉ ከጎንደር ዩንቨርስቲ የማሕበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘ ነው። መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia