የሞስኮ ፍርድ ቤት በሩሲያው ጄኔራል ኪሪሎቭ ግድያ የተጠረጠረን ግለሰብ ማሰሩ ተገለጸየሞስኮ ባስማኒ አካባቢ ፍርድ ቤት በሩሲያው የጦር ኃይሎች የራዲዮሎጂ፣ ኬሚካል እና የባዮሎጂካል መከላከያ ጦር አዛዥ የነበሩትን ሌተናንት ጄነራል ኢጎር ኪሪሎቭ ግድያ የተጠረጠረው አክህማድ ኩርባኖቭ እስከ ጎርጎሮሳውያኑ የካቲት 17 ደረስ በእስር ላይ እንዲቆይ መወሰኑን የስፑትኒክ የዜና ወኪል ዘግቧል። "ፍርድ ቤቱ እስከ ጎርጎሮሳውያኑ የካቲት 17 ድረስ በእስር ላይ እንዲቆይ መርማሪው ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት እንዲያገኝ፣ ውሳኔ ሰጥቷል" ብለዋል ዳኛው።ኪሪሎቭ እና ረዳታቸው ማክሰኞ ጠዋት በሞስኮ በሚገኘው መኖሪያ ህንጻ አጠገብ በተፈጸመ የቦምብ ጥቃት ተገድለዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia