ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ አንድ የአፍሪካ ነዋሪ በእያንዳንዷ ሰከንድ በሚባል ደረጃ የመሰደድ ፍላጎት እንደነበረው የሚያሳይ ጥናት ይፋ ተደረገ

በአማካኝ የአፍሪካ ሁለተኛ ጎረቤት ባለፈው የጎርጎሮሳውያኑ አመት የመሰደድ ፍላጎት እንደነበረው ጥናቶች አመላከቱ አፍሮባሮሜት ተብሎ በሚጠራው የማህበረሰብ ድርጅት ረብዑ እለት ታስቦ የዋለውን አለምአቀፍ የስደተኞች ቀንን በማስመልከት ባወጣው ሪፖርት የስደት ምክንያቶቹ የተሻለ ስራ ፍለጋ እና የኢኮኖማያዊ ጫናን ለማስወገድ የሚደረጉ ጥረቶች ናቸው። " በአማካኝ በጎርጎሮሳዊያኑ 2024 የዳሰሳ ጥናት ከተደረገባቸው 24 የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ 47 በመቶ መላሾች ከሀገር ወጥተው በሌላ ሀገር መስራትን እያሰቡበት ነው ሲሆን ፤ ከመላሾቹ 27 በመቶ "በብዛት" ለመሰደድ እያሰቡበት ነው። የስደት ሀሳቦች በከፍተኛ ደረጃ በላይቤሪያ 78 በመቶ ፣ በጋሚቢያ 68 በመቶ ፣ በካቦ ቨርዴ 64 በመቶ እና በጋና 61 በመቶ ሆኖ መመዝገቡን" ጥናቱ አመላክቷል። በተቃራኒው በታንዛኒያ 8 በመቶ ሰው ስለመሰደድ ያስባል። በአጠቃላይ በጎርጎሮሳዊያኑ ከ2016-2018 የተሰራው የዳሰሳ ጥናት በአፍሪካ ሀገራቸውን ጥለው መሰደድ የሚፈልጉ ሰዎች ቁጥር በ9 በመቶ ሲጨምር በአንዳንድ ሀገራት ቁጥሩ 10 በመቶ ይበልጣል። ይህም ላይቤሪያ በ28 በመቶ ነጥቦች ፣ ሞሪቲየስ በ27 ነጥቦች ፣ ናይጄሪያ በ21 ነጥቦች እና ጋና በ20 ነጥቦች መጨመራቸው ያካትታል። ስደተኞቹ በዋናነት የሚሰደዱት ወደ ሰሜን አሜሪካ (31 በመቶ) እና አውሮፓ (29 በመቶ) ነው። ነገርግን 22 በመቶዉ አፍሪካ ውስጥ ሀገር ቀይረው መሰደድ የሚፈልጉ ናቸው።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
Sputnik
ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ አንድ የአፍሪካ ነዋሪ በእያንዳንዷ ሰከንድ በሚባል ደረጃ የመሰደድ ፍላጎት እንደነበረው የሚያሳይ ጥናት ይፋ ተደረገአፍሮባሮሜትር ተብሎ የሚጠራው የማህበረሰብ ድርጅት ረብዑ እለት ታስቦ የዋለውን ዓለም አቀፍ የስደተኞች ቀንን በማስመልከት ባወጣው ሪፖርት የስደት ምክንያቶቹ የተሻለ ስራ ፍለጋ እና የኢኮኖማያዊ ጫናን ለማስወገድ የሚደረጉ ጥረቶች መሆናቸውን ገልጿል። "በአማካኝ በጎርጎሮሳዊያኑ 2024 የዳሰሳ ጥናት ከተደረገባቸው 24 የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ 47 በመቶ መላሾች ከሀገር ወጥተው በሌላ ሀገር መስራትን የሚያስቡ ሲሆን፤ ከመላሾቹ  27 በመቶ "በብዛት" ለመሰደድ ያስባሉ። የስደት ሀሳቦች በከፍተኛ ደረጃ በላይቤሪያ 78 በመቶ፣ በጋሚቢያ 68 በመቶ፣ በካቦ ቨርዴ 64 በመቶ እና በጋና 61 በመቶ ሆኖ መመዝገቡን" ጥናቱ አመላክቷል። በተቃራኒው በታንዛኒያ 8 በመቶ ሰው ስለመሰደድ ያስባል። በአጠቃላይ በጎርጎሮሳዊያኑ ከ2016-2018 ከተሰራው የዳሰሳ ጥናት ጋር ሲነጻጸር በአፍሪካ ሀገራቸውን ጥለው መሰደድ የሚፈልጉ ሰዎች ቁጥር በ9 በመቶ ሲጨምር በአንዳንድ ሀገራት ቁጥሩ 10 በመቶ ይበልጣል። ይህም የላይቤሪያን 28 በመቶ፣ የሞሪሽየስን በመቶ፣ የናይጄሪያ 21 በመቶ እና የጋናን 20 በመቶ ጭማሪ ያካትታል። ስደተኞቹ በዋናነት የሚሰደዱት ወደ ሰሜን አሜሪካ (31 በመቶ) እና አውሮፓ (29 በመቶ) ነው። 22 በመቶ ግን ወደ ሌላ አፍሪካ መሰደድ የሚፈልጉ ናቸው።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦  APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia