"በደም የተሳሰሩ በፍፁም የማይነጣጠሉ ወንድማማቾች"፦ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር የኡጋንዳ መከላከያ አዛዥን ተቀብለው አነጋገሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የኡጋንዳ ሕዝብ መከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ሙሁዚ ካይኔሩጋባ፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ዛሬ ጠዋት ውይይት አካሂደዋል። የኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በውይይቱ ላይ ተገኝተዋል።የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ልጅ የሆኑት ጄኔራል ካይኔሩጋባ በፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ግብዣ ለስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ይገኛሉ። ካይኔሩጋባ ቅዳሜ እለት አዲስ አበባ ሲደርሱ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባጋሩት ጽሑፍ "ውድ ወንድሜ ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የዘር ሀረጌ መነሻ የሆነችውን ኢትዮጵያን እንድጎበኝ ላደረጉልኝ ግብዣ አመሰግናለሁ። ኡጋንዳ እና ኢትዮጵያ በደም የተሳሰሩ የማይለያዩ ወንድማማቾች ናቸው" ብለዋል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia