የታህሳስ 7 ረፋድ አበይት የዓለም ዜናዎች፦ 🟠 የእስራኤል አየር ኃይል በሶሪያ ላታኪያ እና ታርቱስ ግዛቶች ወታደራዊ ኢላማዎች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ማድረሱን የአካባቢው ምንጮች ገለጹ። 🟠 በኦሃዮ ግዛት የሚገኘው የዩናይትድ ስቴትስ ራይት-ፓተርሰን የጦር ሰፈር የአየር ክልል ያልታወቁ ድሮኖች በመብረራቸው ምክንያት ለጊዜው መዘጋቱን መገናኛ ብዙሃን ዘገቡ። 🟠 የደቡብ ኮሪያ ሕገ-መንግስታዊ ፍርድ ቤት የፕሬዝዳንት ዩን ሱክ-ዩልን የመጀመሪያ ክስ ታህሳስ 18 እንደሚጀምር በሀገር ውስጥ የመገናኛ ብዙሃን ተዘገበ። 🟠 በ2020 በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የሩሲያ እና ሰሜን ኮሪያ መደበኛ የመንገደኞች የባቡር ጉዞ በድጋሚ ጀመረ።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia