የደቡብ አፍሪካ አየር መንገድ አብራሪዎች የስራ ማቆም አድማቸውን አቆሙ

የደቡብ አፍሪካ አየር መንገድ አብራሪዎች የስራ ማቆም አድማቸውን አቆሙ የደቡብ አፍሪካ አየር መንገድ አብራሪዎች የስራ ማቆም አድማ፤ በመጀመሪያው ቀን የአየር መንገዱን ግማሽ ያህል በረራዎች አስተጓጉሎ እንደነበር የደቡብ አፍሪካው ኢኤንሲኤ ዘግቧል። በደመወዝ ድርድር መቋረጥ ምክንያት ሀሙስ የጀመረው አድማ፤ የደቡብ አፍሪካ አየር መንገድ ከአብራሪዎች ማህበር እና ከብሔራዊ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ጋር ስምምነት ላይ መድረሱን ተከትሎ ቆሟል። የደቡብ አፍሪካ አየር መንገድ እስካሁን በጉዳዩ ላይ በይፋ አስተያየት ባይሰጥም፤ ሰፋ ያለ የስራ ሁኔታዎችን ለመፍታት ተጨማሪ ንግግሮችን ለማድረግ መታቀዱን ኢኤንሲኤ ዘግቧል። የስራ ማቆም አድማው ወደ ፐርዝ እና ሳኦ ፓውሎ የሚደረጉ ዓለም አቀፍ በረራዎች እንዲሰረዙ እና የሀገር ውስጥ በረራ እንዲቀንስ አድርጎታል ተብሏል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
Sputnik
የደቡብ አፍሪካ አየር መንገድ አብራሪዎች የስራ ማቆም አድማቸውን አቆሙ የደቡብ አፍሪካ አየር መንገድ አብራሪዎች የስራ ማቆም አድማ፤ በመጀመሪያው ቀን የአየር መንገዱን ግማሽ ያህል በረራዎች አስተጓጉሎ እንደነበር የደቡብ አፍሪካው ኢኤንሲኤ ዘግቧል። በደመወዝ ድርድር መቋረጥ ምክንያት ሀሙስ የጀመረው አድማ፤ የደቡብ አፍሪካ አየር መንገድ ከአብራሪዎች ማህበር እና ከብሔራዊ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ጋር ስምምነት ላይ መድረሱን ተከትሎ ቆሟል። የደቡብ አፍሪካ አየር መንገድ እስካሁን በጉዳዩ ላይ በይፋ አስተያየት ባይሰጥም፤ ሰፋ ያለ የስራ ሁኔታዎችን ለመፍታት ተጨማሪ ንግግሮችን ለማድረግ መታቀዱን ኢኤንሲኤ ዘግቧል። የስራ ማቆም አድማው ወደ ፐርዝ እና ሳኦ ፓውሎ የሚደረጉ ዓለም አቀፍ በረራዎች እንዲሰረዙ እና የሀገር ውስጥ በረራ እንዲቀንስ አድርጎታል ተብሏል።በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia