የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለአፍሪካ አቪዬሽን ልህቀት እያበረከተ ላለው አስተዋፅዖ የዕውቅና ሽልማት ተበረከተለትአየር መንገዱ ሽልማቱን ከአፍሪካ ሲቪል አቪዬሽን ኮሚሽን ተረክቧል። ሽልማቱ የተበረከተው፤ በኮንጎ ሪፐብሊክ ዋና ከተማ ብራዛቪል በተካሄደው 35ኛው የአፍሪካ ሲቪል አቪዬሽን ኮሚሽን ጉባኤ ላይ ነው፡፡ አየር መንገዱ ዕውቅናው የተሰጠው፤ በአፍሪካ በርካታ መዳረሻዎች የበረራ አገልግሎት በመስጠት፤ የአፍሪካ አቪዬሽን ኢንዱስትሪን በማሳደግ ረገድ ለተጫወተው ሚና እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የአፍሪካ ሲቪል አቪዬሽን ኮሚሽን፤ በአፍሪካ ሕብረት ስር የሚተዳደርና የአፍሪካ ሲቪል አቪዬሽን ጉዳዮችን የሚከታተል ልዩ ኤጀንሲ ነው፡፡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia