ባይደን በአታስምስ ሚሳኤሎች ላይ ያስተላለፉት ውሳኔ በግልጽ ኃላፊነት የጎደለው ነው ሲሉ የአርጀንቲና የሶሺዮሎጂ ባለሙያ ለስፑትኒክ ተናገሩ"የባይደን ድርጊት ዩክሬን እና የኔቶ አባል ሀገሮች ሊደርስባቸው የሚችለውን የማይቀር ሽንፈት እርግጠኝነት የሚያሳይ ይመስላል፤ ስለሆነም ዶናልድ ትራምፕ ወደ ስልጣን ከመምጣታቸው በፊት ባሉት ወራት ሩሲያ ለዚህ ድርጊት ምላሽ መስጠቷን ማረጋገጥ ይፈልጋሉ፤ ይህም የጦርነት መባባስ አደጋን ይጨምራል" ሲሉ የፖለቲካ ምሁሩ ጆርጅ ኤልባም (ዶ/ር) ተናግረዋል።የባይደን ውሳኔ በታሪክ ውስጥ "አስቀያሚ ፍርሀት ውስጥ የነበረ ፕሬዝዳንት" ብቻ ሳይሆን መላውን ዓለም ፍጻሚ በሌለው አደገኛ ሁኔታ ውስጥ የጣሉ ሰው ጭምር ያደርጋቸዋል ብለዋል።በተመሳሳይ ጊዜ ሜክሲኮአዊው የዓለም አቀፍ ግንኙነት ባለሙያ ዴቪድ ጋርሲያ ኮንትሬራስ፤ በባይደን የተወሰደው እርምጃ "የዩክሬይን አቋም ለማጠናከር የመጨረሻው የተስፋ መቁረጥ ሙከራ" ነው ብለው ያምናሉ።በትላንትናው ዕለት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ዩክሬይን አታሲምስ የተባለዉን የአሜሪካን ሚሳኤል ተጠቅማ በሩሲያ ውስጥ ጥቃት እንደትፈጽም መፍቀዳቸው ተገልጿል። በመስከረም ወር የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ኬቭ የምዕራባውያንን ረጅም-ርቀት ሚሳኤሎችን በሩሲያ ላይ እንደትጠቀም መፈቀድ ማለት ኔቶ በሩሲያ ፌዴሬሽን ላይ በሚደረገው ጦርነት ቀጥተኛ ተሳታፊ ነው ማለት ነው ብለዋል።ዜናውን በእንግሊዝኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ ለአንድሮይ ስልኮች በዚህ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዩጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia