ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን የፖሊስ ተቋማቶቻቸውን ለማጠናከር እንደተስማሙ የኢትዮጵያ ኢምባሲ አስታወቀ በደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር ነቢል ማህዲ፤ ከደቡብ ሱዳን የፖሊስ ዋና ኢንስፔክተር ጀነራል አተም ማሮል ቢያር ኩክ ጋር ተገናኝተው፤ በቅርቡ በኢትዮጵያ መሰጠት የተጀመረውን የደቡብ ሱዳን መኮንኖች ስልጠና ፕሮግራም ጨምሮ፤ በፖሊስ ዘርፍ ትብብራቸውን ስለማጠናከር ተወያይተዋል። ሁለቱም ሀገራት የፖሊስ አቅማቸውን በወደፊት ትብብር በማሳደግ፤ በሀገራቱ እና በቀጠናው ውስጥ ያለውን ደህንነት እና መረጋጋት ለማሻሻል ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- ለአንድሮይድ ስልኮች በዚህ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia