ቱርክ ከእስራኤል ጋር የነበራት ግንኙነት አቋረጠች

ቱርክ ከእስራኤል ጋር የነበራት ግንኙነት አቋረጠች "በሬሲፕ ታይፕ ኤርዶአን የሚመራው የቱርክ ሪፐብሊክ መንግሥት ከእስራኤል ጋር ያለውን ግንኙነት አይቀጥልም። ከእስራኤል ጋር የነበረንን ንግድ እና ግንኙነት ሙሉ በሙሉ አቋርጠናል። ከፍልስጤም ተገቢ ዓላማ ጎን እስከ መጨረሻው በፅናት እንቆማለን" ሲሉ የቱርክ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ታይፕ ኤርዶአን ከሳዑዲ አረቢያ እና አዘርባጃን ሲመለሱ አውሮፕላን ውስጥ ለጋዜጠኞች ጥያቄ መልስ በሰጡበት ወቅት ተናግረዋል። ቱርክ፤ በጋዛ ሰርጥ የእስራኤል ጥቃት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ፤ የቴል አቪቭን ድርጊት ስታወግዝ እና እስራኤል በፍልስጤም ሲቪሎች ላይ የጅምላ ግድያ እየፈጸመች ነው ስትል ትከሳለች። ሀገሪቱ በተደጋጋሚ የተኩስ አቁም ጥሪ ስታቀርብ እና በእስራኤል ላይ ጫና ስታደርግም ቆይታለች። በግንቦት ወር መጀመሪያ፤ የቱርክ የንግድ ሚኒስቴር ከእስራኤል ጋር የነበረው የንግድ ልውውጥ ሙሉ በሙሉ መቆሙን አስታውቋል። አንካራ፤ ቀደም ብላ ወደ እስራኤል የሚላኩ 54 ሸቀጣ ሸቀጦችን ገድባለች።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- ለአንድሮይድ ስልኮች በዚህ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
Sputnik
ቱርክ ከእስራኤል ጋር የነበራት ግንኙነት አቋረጠች "በሬሲፕ ታይፕ ኤርዶአን የሚመራው የቱርክ ሪፐብሊክ መንግሥት ከእስራኤል ጋር ያለውን ግንኙነት አይቀጥልም። ከእስራኤል ጋር የነበረንን ንግድ እና ግንኙነት ሙሉ በሙሉ አቋርጠናል። ከፍልስጤም ተገቢ ዓላማ ጎን እስከ መጨረሻው በፅናት እንቆማለን" ሲሉ የቱርክ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ታይፕ ኤርዶአን ከሳዑዲ አረቢያ እና አዘርባጃን ሲመለሱ አውሮፕላን ውስጥ ለጋዜጠኞች ጥያቄ መልስ በሰጡበት ወቅት ተናግረዋል። ቱርክ፤ በጋዛ ሰርጥ የእስራኤል ጥቃት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ፤ የቴል አቪቭን ድርጊት ስታወግዝ እና እስራኤል በፍልስጤም ሲቪሎች ላይ የጅምላ ግድያ እየፈጸመች ነው ስትል ትከሳለች። ሀገሪቱ በተደጋጋሚ የተኩስ አቁም ጥሪ ስታቀርብ እና በእስራኤል ላይ ጫና ስታደርግም ቆይታለች። በግንቦት ወር መጀመሪያ፤ የቱርክ የንግድ ሚኒስቴር ከእስራኤል ጋር የነበረው የንግድ ልውውጥ ሙሉ በሙሉ መቆሙን አስታውቋል። አንካራ፤ ቀደም ብላ ወደ እስራኤል የሚላኩ 54 ሸቀጣ ሸቀጦችን ገድባለች።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- ለአንድሮይድ ስልኮች በዚህ APK  ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia