የአፍሪካ ዝሆኖች ቁጥር በ50 ዓመታት ውስጥ በአማካይ በ77 በመቶ መቀነሱን ጥናት አመላከተበአሜሪካውያን ሳይንቲስቶች ጆርጅ ዊትሜየር፣ ቻርልስ ቲ. ቲ ኤድዋርድስ፣ ካትሊን ኤስ. ጎቡሽ በተካሄድ ጥናት መሰረት፤ የጫካ ዝሆኖች ብዛት በአማካይ 90 በመቶ ሲቀንስ የሳቫና ዝሆኖች ብዛት ደግሞ 70 በመቶ ቀንሷል። መረጃው የተገኘው በጎርጎሮሳውያኑ አቆጣጠር በ1964 እና 2016 መካከል በ37 ሀገሮች በ475 ቦታዎች በተደረገ ጥናት ነው።"በበርካታ ሀገራት ብዙ ዝሆኖችን አጥተናል፤ ነገር ግን በሰሜናዊ ሳሀል የአፍሪካ ቀጠና ለምሳሌ በማሊ፣ ቻድ እና ናይጄሪያ ቁጥሩ ከፍተኛ ነው። በከፍተኛ ጫና እና ውስን ጥበቃ ምክንያት ብዛታቸው በከፍተኛ ሁኔታ እንዲመናመን ሆኗል” ሲሉ ጆርጅ ዊትሜየር መግለጻቸውን የምዕራባውያን የዜና አውታር ዘግቧል።በጎርጎሮሳዊያኑ 1989 በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ውሳኔ መሠረት ለጌጣጌጥና ለዕደ ጥበብ የሚውለውን የዝሆን ጥርስ ዓለም አቀፍ ንግድ ሙሉ በሙሉ ታግዷል። በዓለም ዙሪያ ያሉ በርካታ አገሮች፣ የዝሆን ግድያ በሞት ቅጣት ያስቀጣል። ሁሉም የዝሆን ዝርያዎች ለመጥፋት አደጋ የተጋለጡ በመሆናቸው በቀይ መጽሐፍ ዝርዝር ውስጥ ተካተዋል።ዜናውን በእንግሊዝኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦ ለ አንድሮይድ ስልኮች በዚህ APK ፋይልሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia