🪧 በተባባሰው ዚሞዛምቢክ ዚምርጫ ውጀት ተቃውሞ ኹ20 ያላነሱ ሰዎቜ መሞታ቞ው ተነገሹ

🪧 በተባባሰው ዚሞዛምቢክ ዚምርጫ ውጀት ተቃውሞ ኹ20 ያላነሱ ሰዎቜ መሞታ቞ው ተነገሹ ዚገዥው ፍሬሊሞ ፓርቲ ፕሬዝዳንት ዳንኀል ቻፖፀ መስኚሚም 29 በተካሄደው ዚሞዛምቢክ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ 70.67% ድምጜ በማግኘት እንዳሞነፉ መገለጹን ተኚትሎፀ በሀገሪቱ ኹፍተኛ ተቃውሞ ተነስቷል። ሆኖምፀ ሀገሪቱን ሞሜተው ወጥተዋል በሚባሉት ፕሬዝዳንታዊ እጩ ቬናንሢዮ ሞንድላኒ ዚሚመራው ዹተቃዋሚ ፓርቲፀ ምርጫው ተጭበርብሯል በማለት ወጀቱን ውድቅ ያደሚገ ሲሆንፀ ትክክለኛው ዚምርጫ ውጀት እስኪመለስ ድሚስ ተኚታታይ አድማ እና ሕዝባዊ ተቃውሞ እንዲደሚግ ጥሪ አቅርቧል። ኚፖሊስ ጋር በተፈጠሹ ግጭት ኹ20 በላይ ሰዎቜ መሞታ቞ውን እና በመቶዎቜ ዚሚቆጠሩ መቁሰል ወይም መታሰራ቞ውን አምነስቲ ኢንተርናሜናልን ጚምሮ ዚሰብዓዊ መብት ተሟጋቜ ድርጅቶቜ ሪፖርት አድርገዋል። ለተቃውሞ ዚወጡ ሶስት ሰዎቜ እንደተገደሉ እና 66 ሰልፈኞቜ ላይ ጉዳት መድሚሱንፀ ዚማፑቶ ማዕኹላዊ ሆስፒታል ሐሙስ እለት አሚጋግጧል። ዚፍሬሊሞ ባለስልጣናትፀ ህዝባዊ ተቃውሞው ለብሔራዊ ደህንነት ስጋት እና “ዹመፈንቅለ መንግሥት ሙኚራ” ነው በማለት አውግዘውታል። በብሔራዊ ዚ቎ሌቪዥን ጣብያ ቀርበው ንግግር ያደሚጉት ዚፍሬሊሞ ቃል አቀባይ አልሲንዳ ዮ አብሩፀ ዹቀጠለው ዹተቃውሞ ሰልፍ ጥሪ እንዳሳሰባ቞ው በመግለፅፀ ተመሳሳይ ዹተቃውሞ ሰልፎቜ አመፅ ዚሚያበሚታቱ እና መንግሥትን ዚማተራመስ ዓላማ ያላ቞ው ናቾው ብለዋል።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- ለአንድሮይድ ስልኮቜ በዚህ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
Sputnik
🪧 በተባባሰው ዚሞዛምቢክ ዚምርጫ ውጀት ተቃውሞ ኹ20 ያላነሱ ሰዎቜ መሞታ቞ው ተነገሹ ዚገዥው ፍሬሊሞ ፓርቲ ፕሬዝዳንት ዳንኀል ቻፖፀ መስኚሚም 29 በተካሄደው ዚሞዛምቢክ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ 70.67% ድምጜ በማግኘት እንዳሞነፉ መገለጹን ተኚትሎፀ በሀገሪቱ ኹፍተኛ ተቃውሞ ተነስቷል። ሆኖምፀ ሀገሪቱን ሞሜተው ወጥተዋል በሚባሉት ፕሬዝዳንታዊ እጩ ቬናንሢዮ ሞንድላኒ ዚሚመራው ዹተቃዋሚ ፓርቲፀ ምርጫው ተጭበርብሯል በማለት ወጀቱን ውድቅ ያደሚገ ሲሆንፀ ትክክለኛው ዚምርጫ ውጀት እስኪመለስ ድሚስ ተኚታታይ አድማ እና ሕዝባዊ ተቃውሞ እንዲደሚግ ጥሪ አቅርቧል። ኚፖሊስ ጋር በተፈጠሹ ግጭት ኹ20 በላይ ሰዎቜ መሞታ቞ውን እና በመቶዎቜ ዚሚቆጠሩ መቁሰል ወይም መታሰራ቞ውን አምነስቲ ኢንተርናሜናልን ጚምሮ ዚሰብዓዊ መብት ተሟጋቜ ድርጅቶቜ ሪፖርት አድርገዋል። ለተቃውሞ ዚወጡ ሶስት ሰዎቜ እንደተገደሉ እና 66 ሰልፈኞቜ ላይ ጉዳት መድሚሱንፀ ዚማፑቶ ማዕኹላዊ ሆስፒታል ሐሙስ እለት አሚጋግጧል። ዚፍሬሊሞ ባለስልጣናትፀ ህዝባዊ ተቃውሞው ለብሔራዊ ደህንነት ስጋት እና “ዹመፈንቅለ መንግሥት ሙኚራ” ነው በማለት አውግዘውታል። በብሔራዊ ዚ቎ሌቪዥን ጣብያ ቀርበው ንግግር ያደሚጉት ዚፍሬሊሞ ቃል አቀባይ አልሲንዳ ዮ አብሩፀ ዹቀጠለው ዹተቃውሞ ሰልፍ ጥሪ እንዳሳሰባ቞ው በመግለፅፀ ተመሳሳይ ዹተቃውሞ ሰልፎቜ አመፅ ዚሚያበሚታቱ እና መንግሥትን ዚማተራመስ ዓላማ ያላ቞ው ናቾው ብለዋል።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- ለአንድሮይድ ስልኮቜ በዚህ APK  ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia