የሱዳን ጦር አዛዥ የካቢኔ ሽግሽግ አደረጉ፤ አዲስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሾመዋልየሱዳን ጦር አዛዥና የሱዳን ሉአላዊ የሽግግር ምክር ቤት ሊቀመንበር ጄኔራል አብድል ፋታህ አልቡርሃን ጽ/ ቤት እሁድ ዕለት በወጣው መግለጫ፣ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር የነበሩት ሁሴን አዋድ አሊን ከኃላፊነታቸው ተነስተው በአሊ የሱፍ አህመድ መተካታቸውን አስታውቋል።የአዲሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር አሊ የሱፍ አህመድ ለኃላፊነቱ የካበተ ልምዳቸውን ያዋጣሉ ተብሏል። በሱዳን የውጭ ጉዳይ አገልግሎት ውስጥ ከአምስት አስርት ዓመታት በላይ ያገለገሉት አሊ የሱፍ፤ በብራስልስ የአውሮፓ ህብረት የሱዳን አምባሳደር እንዲሁም በቻይና እና በደቡብ አፍሪካ አምባሳደር በመሆን በወሳኝ ኃላፊነቶች በመመደብ አገልግለዋል።በአል ቡርሃን የተፈረመው አዋጅ አዲሱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከመሾሙ በተጨማሪ በንግድ እና አቅርቦት ሚኒስቴር፣ በባህል እና መረጃ ሚኒስቴር እና በሃይማኖታዊ ጉዳዮች እ ሚኒስቴር ላይ ለውጦችን አካቷል።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ ለ አንድሮይድ ስልኮች በዚህ APK ፋይል ሊንክስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia