የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የብሪክስ የመሪዎች ጉባዔ ተሳትፎ ስኬታማ እንደነበር የጽህፈት ቤታቸው የፕሬስ ኃላፊ ገለጹ

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የብሪክስ የመሪዎች ጉባዔ ተሳትፎ ስኬታማ እንደነበር የጽህፈት ቤታቸው የፕሬስ ኃላፊ ገለጹበጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተመራ የሚኒስትሮች ልዑካን ቡድን፤ በሩሲያ ካዛን በተካሄደው 16ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባዔ መሳተፉ የሚታወስ ነው፡፡ ኢትዮጵያ፤ የቡድኑ አባል ከሆነች በኋላ የተሳተፈችበት የመጀመሪያው ጉባዔ እንደሆነ፤ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም ገልጸዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በጉባዔው ላይ በሁለትዮሽ እና በባለብዙ ወገን የምክክር መድረኮች ላይ ውጤታማ ተሳትፎ ማድረጋቸውን አመልክተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ አፍሪካ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ማግኘት እንዳለባት እና ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓቱ እንዲሻሻል፤ በጉባዔው ጥሪ ማቅረባቸውን ተናግረዋል።ከጉባዔው ጎን ለጎን፤ ከብሪክስ አባል እና አባል ለመሆን ከሚፈልጉ ሀገራት መሪዎች ጋር በተደረጉ የሁለትዮሽ ውይይቶች፤ የኢትዮጵያን አቋሞች አንጸባርቀዋል ማለታቸውን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግቧል። መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- ለአንድሮይድ ስልኮች በዚህ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
Sputnik
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የብሪክስ የመሪዎች ጉባዔ ተሳትፎ ስኬታማ እንደነበር የጽህፈት ቤታቸው የፕሬስ ኃላፊ ገለጹበጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተመራ የሚኒስትሮች ልዑካን ቡድን፤ በሩሲያ ካዛን በተካሄደው 16ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባዔ መሳተፉ የሚታወስ ነው፡፡ ኢትዮጵያ፤ የቡድኑ አባል ከሆነች በኋላ የተሳተፈችበት የመጀመሪያው ጉባዔ እንደሆነ፤ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም ገልጸዋል።ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በጉባዔው ላይ በሁለትዮሽ እና በባለብዙ ወገን የምክክር መድረኮች ላይ ውጤታማ ተሳትፎ ማድረጋቸውን አመልክተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ አፍሪካ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ማግኘት እንዳለባት እና ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ስርዓቱ እንዲሻሻል፤ በጉባዔው ጥሪ ማቅረባቸውን ተናግረዋል።ከጉባዔው ጎን ለጎን፤ ከብሪክስ አባል እና አባል ለመሆን ከሚፈልጉ ሀገራት መሪዎች ጋር በተደረጉ የሁለትዮሽ ውይይቶች፤ የኢትዮጵያን አቋሞች አንጸባርቀዋል ማለታቸውን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግቧል። መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- ለአንድሮይድ ስልኮች በዚህ APK  ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia