የምዕራቡ ዓለም ማዕቀብ ሩሲያን ማግለል እንዳልቻለ #BRICS2024 የመሪዎች ጉባኤ አረጋግጧል ሲሉ የደቡብ አፍሪካው ዲፕሎማት ተናገሩ"አሜሪካ እና የአውሮፓ ሀገራት ሩሲያ ላይ በማዕቀብ በመጣል ለማቆም እና ለማግለል ሞክረዋል፤ ሆኖም ግን (በካዛን የተካሄደው የብሪክስ ስብሰባ) ከ 30 በላይ የዓለም መሪዎች የተሳተፉበት መሆኑ ያውም ከ ብሪክስ ህብረት ውጪ ያሉ ሀገራት ተሳትፈዋል። ይህ የሚያሳየው ሌሎች ሀገራት የተባበሩት መንግስታት ቻርተርን መንፈስ ለሚጥስ የአንድ ወገን ማዕቀብ ድጋፍ እንደማይሰጡ ያሳያል " ሲሉ በህንድ የደቡብ አፍሪካ አምባሳደር እና የቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ብሪክስ ሸርፓ አኒል ሱክላል ከቻይናው ሚዲያ ጓንቻ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ላይ ተናግረዋል። በርካታ መሪዎች ለጉባኤው ወደ ሩሲያ ለመምጣት መወሰናቸው የማህበሩን "በአለም አቀፍ ፖለቲካ ውስጥ ጠንካራ ሃይል" መሆኑን ያሳያል። ይህን ጉባኤ በማዘጋጀት ሩሲያ የብሪክስ ሃገራት የመልቲላተራሊዝም መርህን እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቻርተርን መሰረት በማድረግ ፍትሃዊ የሆነ አለምአቀፍ ስርአት ለመገንባት ቁርጠኛ መሆናቸውን አሳይታለች ሲል ሱክላል አፅንኦት ሰጥቶ ተናግሯል።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- ለአንድሮይድ ስልኮች በዚህ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia