የደቡብ አፍሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እስራኤል በሊባኖስ የምትፈጽመው የአየር ጥቃት የሀገሪቱን ሉዓላዊነት የሚጥስ ነው አለ ደቡብ አፍሪካ በሊባኖስ ላይ የተፈጸመውን የቦምብ ጥቃት ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ ህግጋትን የሚጥስ ድርጊት በመሆኑ ታወግዘዋለች ሲል የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመግለጫው አስታውቋል። ፕሪቶሪያ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጥቃቱን ችላ እንዳይልም ጠይቃለች። በመግለጫው ላይ የደቡብ አፍሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እስራኤል በሊባኖስ የምታካሂደውን ወታደራዊ ዘመቻ የማታቆም ከሆነ ቀጠናውን ወደ ከፋ ግጭት ልትከት ትችላለች ሲልም አስጠንቅቋል። በፈረንጆቹ ጥቅምት10 ቀን የእስራኤል ጦር በማዕከላዊ ቤይሩት ባካሄደው ጥቃት ከ20 በላይ ሰዎች እንደሞቱ እና ከ107 በላይ የሚሆኑ ደግሞ መቁሰላቸውን የሊባኖስ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። የእስራኤል ጦር በሊባኖስ ዋና ከተማ መኻል በሚገኙ የመኖሪያ ሰፈሮች የአፓርታማ ህንጻዎች እና ትንንሽ ሱቆች ላይ ደብድባ አካሂዷል።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- ለ iOS በአፕ ስቶር ለአንድሮይድ ስልኮች በዚህ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia