ሩሲያ ኢትዮጵያ ውስጥ ትምህርት ቤት የመክፈት ፍላጎት እንዳላት አስታወቀችይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ ፌዴሬሸን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር በሩሲያ ሴናተር ኒኮላይ ቪላዲሚሮቭ ከተመራው ልዑክ ጋር በተወያዩበት ወቅት ነው፡፡ የፌዴሬሸን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር ኢትዮጵያና ሩሲያ የረጅም ዘመን የታሪክና ባህል ግንኙነት እንዳላቸው በውይይቱ ወቅት አንስተዋል፡፡ አክውም የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል።ኢትዮጵያ በብሪክስ አባል ሀገራት የሚወሰኑ ውሳኔዎችን ተግባራዊ ለማድረግ ተግታ እንደምትሰራም ጠቁመዋል፡፡የሩሲያ ሴናተር ኒኮላይ ቪላዲሚሮቭ በበኩላቸው ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በላይ ለሩሲያ ጠንካራ ወዳጅ ሀገር ነች ብለዋል። ሞስኮ በትምህርት፣ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እና ባህል ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥልና የሩሲያን ትምህርት ቤት ኢትዮጵያ ውስጥ የመክፈት ፍላጎት እንዳላት አንስተዋል።የብሪክስ አባል ሀገራት ሰብሳቢ የሆነችው ሩሲያ ሀገራቱ በትብብርና ቅንጅት እንዲሰሩ አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደምታደርግ ሴናተር ቪላዲሚሮቭ ተናግረዋል። መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- ለ iOS በአፕ ስቶር ለአንድሮይድ ስልኮች በዚህ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia