እስራኤል ወታደራዊ እንቅስቃሴዋን በተቻለ ፍጥነት እንድታቆም ፈረንሳይ ጠየቀች

እስራኤል ወታደራዊ እንቅስቃሴዋን በተቻለ ፍጥነት እንድታቆም ፈረንሳይ ጠየቀችየፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ፅህፈት ቤት በሊባኖስ እና በጋዛ ሰርጥ ያለውን እንቅስቃሴ አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ " ማክሮን እስራኤል ወታደራዊ እንቅስቃሴዋን በተቻለ ፍጥነት እንድታቆም ጠይቀዋል" ብሏል።ፈረንሳይ የሊባኖስን ህዝቦች እና የሀገሪቱን መሰረታዊ ተቋማት ለማገዝ በቅርቡ ጉባኤ እንደምታዘጋጅም መግለጫው አክሎ ገልጿል።ፓሪስ የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት ውሳኔ 1701 በጥብቅ በማክበር የሊባኖስ ግዛት አንድነት እንዲከበር ትፈልጋለች ሲል መግለጫው አመልክቷል። ማክሰኞ ኢራን ወደ ደቡባዊ እና መካከለኛው እስራኤል 400 የሚጠጉ ሚሳኤሎችን መተኮሷ ተዘግቧል። የኢራን አይአርጂሲ በይፋ ባወጣው መግለጫ ጥቃቱ እስራኤል በሃማስ የፖለቲካ ቢሮ ሊቀመንበር ኢስማኢል ሃኒዬህ እና በሂዝቦላህ ዋና ፀሃፊ ሀሰን ናስራላህ ላይ ለፈጸመችው ግድያ ምላሽ ነው ብሏል።ኢራን በእስራኤል ላይ የወሰደችው እርምጃ አብቅቷል፣ነገር ግን እስራኤል ግጭት ብትቀስቀስ ምላሹ የበለጠ ጠንካራ ይሆናል ሲሉ የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተናግረዋል።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- ለ iOS በአፕ ስቶር ለአንድሮይድ ስልኮች በዚህ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
Sputnik
  እስራኤል ወታደራዊ እንቅስቃሴዋን በተቻለ ፍጥነት እንድታቆም ፈረንሳይ ጠየቀችየፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ፅህፈት ቤት በሊባኖስ እና በጋዛ ሰርጥ ያለውን እንቅስቃሴ አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ " ማክሮን እስራኤል ወታደራዊ እንቅስቃሴዋን በተቻለ ፍጥነት እንድታቆም ጠይቀዋል" ብሏል።ፈረንሳይ የሊባኖስን ህዝቦች እና የሀገሪቱን መሰረታዊ ተቋማት ለማገዝ በቅርቡ ጉባኤ እንደምታዘጋጅም መግለጫው አክሎ ገልጿል።ፓሪስ የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት ውሳኔ 1701 በጥብቅ በማክበር የሊባኖስ ግዛት አንድነት እንዲከበር ትፈልጋለች ሲል መግለጫው አመልክቷል። ማክሰኞ ኢራን ወደ ደቡባዊ እና መካከለኛው እስራኤል 400 የሚጠጉ ሚሳኤሎችን መተኮሷ ተዘግቧል። የኢራን አይአርጂሲ በይፋ ባወጣው መግለጫ ጥቃቱ እስራኤል በሃማስ የፖለቲካ ቢሮ ሊቀመንበር ኢስማኢል ሃኒዬህ እና በሂዝቦላህ ዋና ፀሃፊ ሀሰን ናስራላህ ላይ ለፈጸመችው ግድያ ምላሽ ነው ብሏል።ኢራን በእስራኤል ላይ የወሰደችው እርምጃ አብቅቷል፣ነገር ግን እስራኤል ግጭት ብትቀስቀስ ምላሹ የበለጠ ጠንካራ ይሆናል ሲሉ የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተናግረዋል።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- ለ iOS በአፕ ስቶር ለአንድሮይድ ስልኮች በዚህ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia