ማሊ ብሪክስን ለመቀላቀል ፍላጎት እንዳላት ገለጸች “አሁን ካለው የባለብዙ ወገን ትብብር አወቃቀር አንጻር ብሪክስ አስደሳች አማራጭ መሆኑን እንገነዘባለን” ሲሉ የማሊ የኢኮኖሚ ሚኒስትር አሉሴኒ ሳኑ በሞስኮ በተካሄደው የሩሲያ የኢነርጂ ሳምንት 2024 ላይ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረው ነበር። "ብሪክስ የሁሉኑም ሀገራት በተለይም የሳህል ሀገራት ቡርኪናፋሶ፣ ማሊ እና ኒጀርን ወቅታዊ ነባራዊ ሁኔታን ከግምት ውስጥ ያስገባል" ሲሉ ሚኒስትሩ አበክረው ተናግረዋል። ቡርኪናፋሶ ቡድኑን ለመቀላቀል ያላትን ፍላጎት አስመልክቶ አስተያየት የሰጡት ሚኒስትሩ፦ "በርካታ ሀገራት እንደ ቡርኪናፋሶና ሌሎችም ማሊንም ጨምሮ በብሪክስ ላይ እያሳዩት ያለው ፍላጎት ከአፍሪካ ሀገራት አንጻር ሚዛናዊነት ሰለሚጎድለው በሁሉም ከሚወገዘው ወቅታዊ ትብብር ጎን ለጎን የሚኖር ሌላ ቡድን በመሆኑ ነው" ብለዋል።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- ለ iOS በአፕ ስቶር ለአንድሮይድ ስልኮች በGoogle Play ወይም በዚህ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia