የመንግሥታቱ ድርጅት የሰላም ማስከበር ኦፕሬሽን የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪዎች እያደረጉት ያለውን አስተዋጽኦ አወደሰ

የመንግሥታቱ ድርጅት የሰላም ማስከበር ኦፕሬሽን የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪዎች እያደረጉት ያለውን አስተዋጽኦ አወደሰ ይህ የተገለጸው በኒውዮርክ እየተካሄደ ከሚገኘው 79ኛው የተመድ ጠቅላላ ጉባዔ ጎን ለጎን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰላም ኦፕሬሽን ረዳት ዋና ፀሐፊ ዣን ፒዬር ለክሮ ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት ነው። ሁለቱ ሀላፊዎች በምስራቅ አፍሪካ ቀጠና ሰላም ማስከበርን በተመለከቱ ቁልፍ ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውን የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። የአፍሪካ ህብረት የሶማሊያ የሽግግር ተልዕኮን (አትሚስ) በታህሳስ 2024 ለማጠናቀቅ የሚደረገውን ዝግጅት አስመልክቶ ሚኒስትር አጽቀሥላሴ ሀገራቸው በቀጠናው ሽብርተኝነትን ለመዋጋት ቁርጠኝ እንደሆነች ገልጸዋል። ማንኛውም ከአትሚስ በኋላ የሚደረግ ስምሪት በግዳጅ፣ በመጠን፣ በገንዘብና በቅንጅት ረገድ ጥንቃቄ እንደሚያስፈልገው አሳስበዋል። የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የውጭ ኃይላት የሚያቀርቡት ጦር መሳሪያ በአካባቢው ያለውን የጸጥታ ሁኔታ የማባባስ እና አሸባሪዎች እጅ ላይ የመውደቅ እድሉ ከፍተኛ ነው በማለት ስጋታቸውን ገልጸዋል።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- ለ iOS በአፕ ስቶር ለአንድሮይድ ስልኮች በGoogle Play ወይም በዚህ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
Sputnik
የመንግሥታቱ ድርጅት የሰላም ማስከበር ኦፕሬሽን የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪዎች እያደረጉት ያለውን አስተዋጽኦ አወደሰ ይህ የተገለጸው በኒውዮርክ እየተካሄደ ከሚገኘው 79ኛው የተመድ ጠቅላላ ጉባዔ ጎን ለጎን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰላም ኦፕሬሽን ረዳት ዋና ፀሐፊ ዣን ፒዬር ለክሮ ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት ነው። ሁለቱ ሀላፊዎች በምስራቅ አፍሪካ ቀጠና ሰላም ማስከበርን በተመለከቱ ቁልፍ ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውን የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። የአፍሪካ ህብረት የሶማሊያ የሽግግር ተልዕኮን (አትሚስ) በታህሳስ 2024 ለማጠናቀቅ የሚደረገውን ዝግጅት አስመልክቶ ሚኒስትር አጽቀሥላሴ ሀገራቸው በቀጠናው ሽብርተኝነትን ለመዋጋት ቁርጠኝ እንደሆነች ገልጸዋል። ማንኛውም ከአትሚስ በኋላ የሚደረግ ስምሪት በግዳጅ፣ በመጠን፣ በገንዘብና በቅንጅት ረገድ ጥንቃቄ እንደሚያስፈልገው አሳስበዋል። የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የውጭ ኃይላት የሚያቀርቡት ጦር መሳሪያ በአካባቢው ያለውን የጸጥታ ሁኔታ የማባባስ እና አሸባሪዎች እጅ ላይ የመውደቅ እድሉ ከፍተኛ ነው በማለት ስጋታቸውን ገልጸዋል።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- ለ iOS በአፕ ስቶር ለአንድሮይድ ስልኮች በGoogle Play ወይም በዚህ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia