በሴኔጋል የባህር ዳርቻ በሰጠመው ጀልባ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 39 መድረሱን የሀገሪቱ ባህር ኃይል አስታወቀ በጀልባ መገልበጥ አደጋው 26 ሰዎች እንደሞቱ የባህር ኃይሉ ማክሰኞ እለት አስታውቋል። "ጀልባው የተገለበጠው ምቦር ከተማ አቅራቢያ ነው። በተደረገው ፍለጋ… 39 አስከሬኖች ተገኝተዋል። የሀገሪቱ ባህር ኃይል ፍለጋውን ቀጥሏል" ሲል ባህር ኃይሉ ሐሙስ እለት በኤክስ የትስስር ገጹ ገልጿል። ወደ አውሮፓ ለመጓዝ ሙከራ ያደረገው ከ200 በላይ ሰዎችን ያሳፈረው ጀልባ ከሴኔጋል የባህር ዳርቻ በግምት 3 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከእሁድ ምሽት እስከ ሰኞ ባለው ግዜ ውስጥ ተገልብጧል።ዜናውን በእንግሊዘኛ ያንብቡ መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፡- ለ iOS በአፕ ስቶር ለአንድሮይድ ስልኮች በGoogle Play ወይም በዚህ APK ፋይል ሊንክ ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia