ኒጀር ከአሸባሪዎች ጋር ግንኙነት አላቸው የተባሉ ወደ 250 የሚጠጉ ሰዎችን በቁጥጥር ስር አዋለች የኒጀር የህግ አስከባሪ ኤጀንሲዎች በወሰዱት እርምጃ ቁጥጥር ስር የዋሉት ሰዎት በናይጄሪያ እና ማሊ አዋሳኝ አካባቢዎች መሆኑን የኒጀር ጦር አስታውቋል።በቁጥጥር ስር የዋሉት የአሸባሪው ቡድን ቦኮ ሃራም* እና የጀማአ ኑስርት አል-ኢስላም ወል ሙስሊም* ታጣቂዎች ሲሆኑ፣ በአካባቢ ለብዙ አመታት ሲንቀሳቀሱ ነበር። በቁጥጥር ስር ከዋሉት መካከል በርካታ የውጭ ሀገራት ዜጎች እንደሚገኙበት የተገለፀ የኒጀር ባለስልጣናት ግን ዜግነታቸውን ከመግለፅ ተቆጥበዋል። የጸጥታ አካላት ከፍተኛ መጠን ያለው አደንዛዥ እጽ ከወንጀለኞቹ በቁጥጥር ስር አውለዋል።ዘመቻው በክልሉ ውስጥ አሸባሪዎችን እና የወንጀል ኔትወርኮችን ለማጥፋት ያለመ መጠነ ሰፊ ስልታዊ እርምጃዎች አካል ነው።* የአሸባሪ ድርጅቶች በሩሲያ እና በሌሎች በርካታ ግዛቶች በህግ ታግደዋል።ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia