በሶማሊያ ወደ አዲስ የሰላም ድጋፍ ተልዕኮ የሚደረገው ሽግግር ቀጠናውን በአደጋ የተሞላ እንደሚያደርገው የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት በመግለጫው እንዳስታወቀው ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ብሄራዊ ደህንነቷን አደጋ ላይ የሚጥሉ ለውጦችን በንቃት እየተከታተለች ነው።ኢትዮጵያ በጎረቤት ሀገር ሶማሊያ ጠንካራ መንግስት እንዲኖር እና ሰላማዊ ዜጎችን ከአልሸባብ ጥቃት ለመጠበቅ ላለፉት በርካታ አመታት በሶማሊያ ወታደሮቿን አሰማርታለች።የአፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከአፍሪካ ህብረት የሽግግር ተልዕኮ በሶማሊያ (ኤቲኤምኤስ) ወደ አዲስ የሰላም ድጋፍ ተልዕኮ ለመሸጋገር እየተዘጋጁ ባሉበት ወቅት፣ ቀጠናው ግን ወደ ማይታወቅ ውሃ እየገባ ነው ሲል መግለጫው አመልክቷል።"ሌሎች ተዋናዮች ክልሉን ለማተራመስ እርምጃ እየወሰዱ ባለበት ወቅት ኢትዮጵያ ዝም ብላ ልታይ አትችልም" ሲሉ ቃል አቀባዩ ተናግረዋል።ሚኒስቴሩ መግለጫውን የሰጠው ግብፅ ከሶስት አስርት አመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ሶማሊያ የጦር መሳሪያ መላኳ ከተሰማ በኋላ ነው።በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ ግብፅ ከሞቃዲሾ ጋር የጸጥታ ስምምነት የተፈራረመች ሲሆን በሶማሊያ አዲስ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ወታደሮቿን ለመላክ ፈቃደኛ መሆኗንም ገልጻለች።ኢትዮጵያ አሁንም ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ በመፍታት ከሶማሊያ ህዝብና ከአለም አቀፉ ማህበረሰብ ጋር በመሆን በቀጠናው ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ቁርጠኛ አቋም እንዳላት ጠቁማለች።* አልሻባብ የተሰኘው ድርጅት በሩሲያ እና በሌሎች ሀገራት ታግዷልስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia