በማዕከላዊ ናይጄሪያ በደረሰ አሳዛኝ ጥቃት 13 ሰዎች መሞታቸው ተሰማ

በማዕከላዊ ናይጄሪያ በደረሰ አሳዛኝ ጥቃት 13 ሰዎች መሞታቸው ተሰማ እሮብ እለት በቦኮ ሃራም ታጣቂዎች የተፈጸመ ሳይሆን አይቀርም በተባለ አሰቃቂ ጥቃት ፤ በሺሮ ወረዳ አንጉዋን ማይ-ጊሮ ማህበረሰብ አባላት የሆኑ ሶስት ሴቶችን ጨምሮ 13 ገበሬዎች ተገድለዋል። ታጣቂዎቹ በሞተር ሳይክሎች መጥተው የግብርና ሰራተኞች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት የፈፀሙ ሲሆን አብዛኞቹ ጭንቅላታቸው ላይ በጥይት ተመትተዋል ሲል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና የጸጥታ ምንጮችን ጠቅሰው የምዕራባዊያን መገናኛ ብዙሃን ዘግቧል።የኒጀር ግዛት ተጠባባቂ ገዥ የሆኑት ያኩቡ ጋርባ በፀጥታ አካላት ላይ ጥልቅ ምርመራ እንደሚካሄድ አረጋግጠዋል።በተጨማሪም ተጎጂዎቹ ለማዕድን ፍለጋ እንደሚሄዱ በማህበራዊ ሚዲያ የሚናፈሰው ወሬ የተሳሳተ መሆኑን ገልፀው፤ ተጎጂዎቹ በእውነቱ በተፈናቃዮች ካምፕ ውስጥ የነበሩ እና ወደ አንጉዋን ማይ-ጌሮ ለእርሻ ስራ ለመሄድ የተዘጋጁ መሆናቸውን አብራርተዋል።ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
Sputnik
በማዕከላዊ ናይጄሪያ በደረሰ አሳዛኝ ጥቃት 13 ሰዎች መሞታቸው ተሰማ እሮብ እለት በቦኮ ሃራም ታጣቂዎች የተፈጸመ ሳይሆን አይቀርም በተባለ አሰቃቂ ጥቃት ፤ በሺሮ ወረዳ አንጉዋን ማይ-ጊሮ ማህበረሰብ አባላት የሆኑ ሶስት ሴቶችን ጨምሮ 13 ገበሬዎች ተገድለዋል። ታጣቂዎቹ በሞተር ሳይክሎች መጥተው የግብርና ሰራተኞች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት የፈፀሙ ሲሆን አብዛኞቹ ጭንቅላታቸው ላይ በጥይት ተመትተዋል ሲል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና የጸጥታ ምንጮችን ጠቅሰው የምዕራባዊያን መገናኛ ብዙሃን ዘግቧል።የኒጀር ግዛት ተጠባባቂ ገዥ የሆኑት ያኩቡ ጋርባ በፀጥታ አካላት ላይ ጥልቅ ምርመራ እንደሚካሄድ አረጋግጠዋል።በተጨማሪም ተጎጂዎቹ ለማዕድን ፍለጋ እንደሚሄዱ በማህበራዊ ሚዲያ የሚናፈሰው ወሬ የተሳሳተ መሆኑን ገልፀው፤ ተጎጂዎቹ በእውነቱ በተፈናቃዮች ካምፕ ውስጥ የነበሩ እና ወደ አንጉዋን ማይ-ጌሮ ለእርሻ ስራ ለመሄድ የተዘጋጁ መሆናቸውን አብራርተዋል።ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia