የነሐሴ 13 ምሽት ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች፦

የነሐሴ 13 ምሽት ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች፦ 🟠 የሩሲያ እና አዘርባጃን ፕሬዝዳንቶች ካካሄዱት ውይይት በኋላ በርካታ የጋራ ሰነዶችን ተፈራርመዋል። 🟠 ከኩርስክ ክልል ወረራ በኋላ ከኪዬቭ ጋር ምንም ዓይነት ንግግር ሊኖር እንደማይችል የሩሲያው ፕሬዝዳንት በግልፅ ተናግረዋል ያሉት ላቭሮቭ ከኪዬቭ ጋር ለመነጋገር ግኑኝነት ተጀምሯል የሚሉ ሪፖርቶች ያልተረጋገጡ ወሬዎች ናቸው ብለዋል። 🟠 የዴንማርክ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሃላፊ ዩክሬን የዴንማርክ ጦር መሳሪያዎችን ተጠቅማ የሩሲያን ግዛት ልታጠቃ እንደምትችል ተናግረዋል። 🟠 ሞስኮ ሩሲያ ላይ የጥላቻ መስመር በሚያራምዱ የብሪታኒያ የጥናት ተቋማት እና አማካሪ ኤጀንሲ ተወካዮች ላይ የግል ማዕቀብ እየጣለች እንደሆነ የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። 🟠 የጀርመን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በርሊን የኖርድ ስትሪም ፍንዳታን በተመለከተ ለሞስኮ መረጃ እየሰጠች ነው ቢልም የምርመራውን ጊዜያዊ ውጤት ግን ሳያሳውቅ ቀርቷል። 🟠 ሩሲያ የምዕራባውያን ጋዜጠኞች ወደ ግዛቷ በህገ-ወጥ መንገድ ሲገቡ እየመዘገበች እንደሆነ እና ህግ በጣሱት ላይ እርምጃ እንደምትወስድ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። 🟠 "የብሪታንያ ቢል ጌትስ" እየተባለ የሚጠራው ባለብዙ ሚልየኔር ማይክ ሊንች በሲሲሊ የባህር ዳርቻ ከቱሪስቶች ጋር ይጓዝ የነበረበት መርከብ በመስጠሙ እንደጠፋ የምዕራቡ ዓለም መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
Sputnik
የነሐሴ 13 ምሽት ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች፦ 🟠 የሩሲያ እና አዘርባጃን ፕሬዝዳንቶች ካካሄዱት ውይይት በኋላ በርካታ የጋራ ሰነዶችን ተፈራርመዋል። 🟠 ከኩርስክ ክልል ወረራ በኋላ ከኪዬቭ ጋር ምንም ዓይነት ንግግር ሊኖር እንደማይችል የሩሲያው ፕሬዝዳንት በግልፅ ተናግረዋል ያሉት ላቭሮቭ ከኪዬቭ ጋር ለመነጋገር ግኑኝነት ተጀምሯል የሚሉ ሪፖርቶች ያልተረጋገጡ ወሬዎች ናቸው ብለዋል። 🟠 የዴንማርክ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሃላፊ ዩክሬን የዴንማርክ ጦር መሳሪያዎችን ተጠቅማ የሩሲያን ግዛት ልታጠቃ እንደምትችል ተናግረዋል። 🟠 ሞስኮ ሩሲያ ላይ የጥላቻ መስመር በሚያራምዱ የብሪታኒያ የጥናት ተቋማት እና አማካሪ ኤጀንሲ ተወካዮች ላይ የግል ማዕቀብ እየጣለች እንደሆነ የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። 🟠 የጀርመን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በርሊን የኖርድ ስትሪም ፍንዳታን በተመለከተ ለሞስኮ መረጃ እየሰጠች ነው ቢልም የምርመራውን ጊዜያዊ ውጤት ግን ሳያሳውቅ ቀርቷል። 🟠 ሩሲያ የምዕራባውያን ጋዜጠኞች ወደ ግዛቷ በህገ-ወጥ መንገድ ሲገቡ እየመዘገበች እንደሆነ እና ህግ በጣሱት ላይ እርምጃ እንደምትወስድ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። 🟠 "የብሪታንያ ቢል ጌትስ" እየተባለ የሚጠራው ባለብዙ ሚልየኔር ማይክ ሊንች በሲሲሊ የባህር ዳርቻ ከቱሪስቶች ጋር ይጓዝ የነበረበት መርከብ በመስጠሙ እንደጠፋ የምዕራቡ ዓለም መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia