ዛምቢያ ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር የሚያዋስናትን ድንበር ከፈተችድንበሩ በሳምንቱ መጨረሻ በተቃውሞ ሰልፎች ሳቢያ ተዘግቶ ነበር፤ ድንበሩ ለዓለማችን ሁለተኛዋ የመዳብ ምርት የኤክስፖርተር ወሳኝ መስመር ነው። "ትላንት ምሽት እ.አ.አ ነሐሴ 12 2024 የዛምቢያ እና የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የንግድ ሚኒስትሮች እንደ እህትማማች ሀገር ለረጅም ጊዜ የቆዩ የንግድ ፕሮቶኮሎችን ለማክበር እና አንዱ በሌላው ላይ ምንም አይነት ማዕቀብ ላይ የተስማሙ ሲሆን፤ ይህም የአለም ንግድ ድርጅት ፕሮቶኮሎችን ባከበር መልኩ ለሁሉም ነጋዴዎች እና መሳሪያዎቻቸውን ደህንነትን ማስጠበቅን ይመጨምራል።የዛምቢያ ንግድ ሚኒስትር ቺፖካ ሙሌንጋ ከሁለቱም ሀገራት የንግድ ሚኒስቴሮች የተውጣጡ የንግድ ኮሚቴ ቀደም ብለው የተነሱት ማነቆዎች ለመፍታት ይሰራሉ።ድንበሩ የተዘጋው በኮንጎ የድንበር ከተማ በሆነችው ካሱምባሌሳ የተካሄደውን ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ ሲሆን፤ ኮንጎ ከውጭ የሚገቡ የለስላሳ መጠጦች እና ቢራዎች ላይ እገዳ በመጣሏ ምክንያት ነው። ሙሌንጋ ይህንን ያስታወቁት በኮንጎ አጓጓዦች በኩል ለተነሳው ተቃውሞ ምላሽ ለመስጠት ነው።ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia