በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ሁለት ቋሚ መቀመጫዎችን እንደምትፈልግ የሴራሊዮን ፕሬዝዳንት ተናገሩ

በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ሁለት ቋሚ መቀመጫዎችን እንደምትፈልግ የሴራሊዮን ፕሬዝዳንት ተናገሩአፍሪካ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ፍትሃዊ ውክልና እና ትርጉም ያለው ተሳትፎን የሚያረጋግጥ የተሃድሶ ራዕይ እና ሞዴል በግልፅ እና አሳማኝ በሆኑ ምክንያቶች ሳቢያ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ሁለት ቋሚ መቀመጫዎች እና ተጨማሪ ሁለት ተለዋጭ መቀመጫዎች ያስፈልጓታል ሲሉ የሴራሊዮን ፕሬዝዳንት ጁሊየስ ማዳ ባዮ በኒውዮርክ በተካሄደው የፀጥታው ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ተናግረዋል።"የለውጡ ጊዜ አሁን ነው። አፍሪካ ድምፅን በድምፅ የመሻር ሥልጣን(የቪቶ ሥልጣን) እንዲቀር ወይም ይህ ሥልጣን ለሁሉም አዲስ ቋሚ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት አባላት እንዲሰጥ ጥሪዋን ታስተላልፋለች" ያሉ ሲሆን አክለውም "የአፍሪካ ድምጽ ሊሠማ ይገባል። የፍትህና የፍትሃዊነት ጥያቄዎች መመለስ ይባቸዋል። "ብለዋል።ባዮ በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት ማሻሻያ ዙሪያ የአፍሪካ ህብረት ያቋቋመውን የአስር ሀገራት መሪዎች ኮሚቴ አስተባባሪ ሆነው እያገለገሉ ይገኛሉ።ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
Sputnik
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ሁለት ቋሚ መቀመጫዎችን እንደምትፈልግ የሴራሊዮን ፕሬዝዳንት ተናገሩአፍሪካ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ፍትሃዊ ውክልና እና ትርጉም ያለው ተሳትፎን የሚያረጋግጥ የተሃድሶ ራዕይ እና ሞዴል በግልፅ እና አሳማኝ በሆኑ ምክንያቶች ሳቢያ በፀጥታው ምክር ቤት ውስጥ ሁለት ቋሚ መቀመጫዎች እና ተጨማሪ ሁለት ተለዋጭ መቀመጫዎች ያስፈልጓታል ሲሉ የሴራሊዮን ፕሬዝዳንት ጁሊየስ ማዳ ባዮ በኒውዮርክ በተካሄደው የፀጥታው ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ተናግረዋል።"የለውጡ ጊዜ አሁን ነው። አፍሪካ ድምፅን በድምፅ የመሻር ሥልጣን(የቪቶ ሥልጣን) እንዲቀር ወይም ይህ ሥልጣን ለሁሉም አዲስ ቋሚ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት አባላት እንዲሰጥ ጥሪዋን ታስተላልፋለች" ያሉ ሲሆን አክለውም "የአፍሪካ ድምጽ ሊሠማ ይገባል። የፍትህና የፍትሃዊነት ጥያቄዎች መመለስ ይባቸዋል። "ብለዋል።ባዮ በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት ማሻሻያ ዙሪያ የአፍሪካ ህብረት ያቋቋመውን የአስር ሀገራት መሪዎች ኮሚቴ አስተባባሪ ሆነው እያገለገሉ ይገኛሉ።ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia