ከ83 ሀገራት የተውጣጣ የልዑካን ቡድን ሩሲያ ውስጥ በሚካሄደው አርሚ-2024 መድረክ እንደሚሳተፍ ተገለጸ ሞስኮ አቅራቢያ በምትገኘው ኩቢንካ ከተማ ዛሬ ሰኞ በሚጀምረው የወታደራዊ ትብብር መድረክ ቢያንስ 39 ልዑካን በመከላከያ ኤጄንሲ ኃላፊዎች እና በጠቅላይ ኤታማዦር ሹሞች ይወከላሉ። በውይይት መድረኩ ከ120 በላይ የውጭ ኩባንያ ተወካዮች በመሳተፍ ላይ መሆናቸው ተጠቅሷል። ብሔራዊ ኤግዚቢሽኖች እና የመከላከያ ኢንተርፕራይዝ የግል ድንኳኖች በቤላሩስ ፣ ኢራን ፣ ህንድ እና ቻይና ተቋቁመዋል። በአጠቃላይ ከ20 ሺህ በላይ ወታደራዊ ናሙናዎች እና ባለ ሁለት ተግባር ምርቶች በመድረኩ ይቀርባሉ። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia