በእስራኤል እና ሃማስ መካከል አዲስ ዙር ድርድር ነሐሴ 9 ሊካሄድ እንደሚችል ተገለጸ ዩናይትድ ስቴትስ፣ ኳታር እና ግብፅ በጋራ ባወጡት መግለጫ መሰረት በእስራኤል እና ሃማስ መካከል አስቸኳይ ድርድር በዶሃ ወይም ካይሮ ይካሄዳል። በሶስቱ ሀገራት መሪዎች የተፈረመው ሰነድ "ቀሪ ክፍተቶችን በሙሉ" ማጥበብ እና በጋዛ ያለ "ተጨማሪ መዘግየት" የተኩስ አቁም እንዲደረግ ሃሳብ አቅርቧል። ዩናይትድ ስቴትስ፣ ኳታር እና ግብፅ "የመዋቅራዊ ስምምነት ላይ ለመድረስ ለወራት ሲሰሩ ቆይተው ተግባራዊ ዝርዝሮች ብቻ ቀርተውት ጠረጴዛ ላይ ቀርቧል" ሲል ገልጿል መግለጫው። ሀገራቱ "ለረጅም ጊዜ በስቃይ ለነበሩት የጋዛ ህዝቦች እንዲሁም ለረጅም ጊዜ ታግተው ለነበሩት እና ቤተሰቦቻቸው አፋጣኝ እፎይታ ለማምጣት ጊዜው አሁን ነው" ብለዋል። የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ፅህፈት ቤት ነሐሴ 9 በሚደረገው ድርድር ላይ ለመገኘት የልዑካን ቡድን ለመላክ ዝግጁ እንደሆኑ ያስታወቁ ሲሆን ሃማስ እስካሁን ምላሽ አልሰጠም። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia