ፑቲን በእስረኞች ልውውጡ "በጣም ጥሩ ስምምነት" መፈፀማቸውን ዶናልድ ትራምፕ አመኑ

ፑቲን በእስረኞች ልውውጡ "በጣም ጥሩ ስምምነት" መፈፀማቸውን ዶናልድ ትራምፕ አመኑ "በነገራችን ላይ ቭላድሚር ፑቲን ሌላ በጣም ጥሩ ስምምነት በማሳካቱ እንኳን ደስ አለህ ልለው እፈልጋለሁ" ሲሉ የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአትላንታ ጆርጂያ በተካሄደ የምርጫ ዘመቻ ቅስቀሳ ላይ ተናግረዋል። በተመሳሳይ በእስረኛ ልውውጡ ደስተኛ እንዳልሆኑ ገልፀው አሁን ያለው የአሜሪካ አስተዳደር በስምምነቱ "አስከፊ" ስህተቶችን እንደሰራ አንስተዋል። ትራምፕ የጆ ባይደን አስተዳደር ስምምነት ላይ መድረሱን ቀደም ሲል የተቹ ሲሆን ይዘቱን በተመለከተ እና ለሩሲያ የገንዘብ ክፍያ ተከፍሏል የሚል ጥርጣሬያቸውን አንስተው ጥያቄዎችን አቅርበዋል። ሐሙስ ዕለት ዩናይትድ ስቴትስ፣ ሩሲያ፣ ጀርመን እና ሌሎች ምዕራባውያን ሀገራት የ24 ሰዎች የእስረኛ ልውውጥ ስምምነት ላይ የደረሱ ሲሆን ይህም ከቀዝቃዛው ጦርነት በኋላ ትልቁ የእስረኞች ልውውጥ ስምምነት ነው። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
Sputnik
ፑቲን በእስረኞች ልውውጡ "በጣም ጥሩ ስምምነት" መፈፀማቸውን ዶናልድ ትራምፕ አመኑ "በነገራችን ላይ ቭላድሚር ፑቲን ሌላ በጣም ጥሩ ስምምነት በማሳካቱ እንኳን ደስ አለህ ልለው እፈልጋለሁ" ሲሉ የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአትላንታ ጆርጂያ በተካሄደ የምርጫ ዘመቻ ቅስቀሳ ላይ ተናግረዋል። በተመሳሳይ በእስረኛ ልውውጡ ደስተኛ እንዳልሆኑ ገልፀው አሁን ያለው የአሜሪካ አስተዳደር በስምምነቱ "አስከፊ" ስህተቶችን እንደሰራ አንስተዋል። ትራምፕ የጆ ባይደን አስተዳደር ስምምነት ላይ መድረሱን ቀደም ሲል የተቹ ሲሆን ይዘቱን በተመለከተ እና ለሩሲያ የገንዘብ ክፍያ ተከፍሏል የሚል ጥርጣሬያቸውን አንስተው ጥያቄዎችን አቅርበዋል። ሐሙስ ዕለት ዩናይትድ ስቴትስ፣ ሩሲያ፣ ጀርመን እና ሌሎች ምዕራባውያን ሀገራት የ24 ሰዎች የእስረኛ ልውውጥ ስምምነት ላይ የደረሱ ሲሆን ይህም ከቀዝቃዛው ጦርነት በኋላ ትልቁ የእስረኞች ልውውጥ ስምምነት ነው። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia