ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ የዩክሬን ጦር 1,930 የሚደርሱ ወታደሮችን እንዳጣ የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ የሚኒስቴሩ ዕለታዊ ሪፖርት ተጨማሪ መግለጫዎች፡- 🟧 የሰሜን ጦር ቡድን በካርኮቭ ክልል ሶስት የዩክሬን ብርጌዶችን ድል አድርጎ የዩክሬን ጦር 205 የሚደርሱ ወታደሮችን አጥቷል። 🟧 በምእራብ የጦር ቡድን የኃላፊነት ቦታ የዩክሬን ሃይሎች 540 ወታደሮችን ከስትራይከር ታጣቂ ተሽከርካሪ ጋር አጥተዋል። 🟧 የሩሲያ አየር መቃወሚያ ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ አምስት ሂማርስ ሮኬቶችን፣ ሁለት ሀመር ቦንቦችን እንዲሁም ከልዩ ዘመቻው ክልል ውስጥ የተመቱትን አስራ ሁለት ድሮኖችን ጨምሮ በአጠቃላይ ሰላሳ አራት ድሮኖችን መትቶ ጥሏል። 🟧 በደቡብ የጦር ቡድን የኃላፊነት ዞን የዩክሬን ኃይሎች እስከ 560 የሚደርሱ ወታደሮችን አጥተዋል። 🟧 የደቡብ ጦር ቡድን ልዩ ግዳጅ የተሰጠውን “አዞቭ*” ብርጌድን ጨምሮ አምስት የዩክሬን ብርጌዶችን ድል አድርጓል። 🟧 የሩሲያ ጦር ዩናይትድ ስቴትስ ሰሩን የፓትሪዮት ሳም ራዳር ጣቢያን ደብድቧል። 🟧 የዩክሬን ጦር በማእከላዊ የጦር ቡድን የኃላፊነት ቦታ ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ 385 የሚሆኑ ወታደሮችን አጥቷል። 🟧 የምስራቅ ጦር ቡድን ባለፉት ቀናት የግንባር ቁመናውን ያሻሻለ ሲሆን ዩክሬን 140 የሚደርሱ ወታደሮችን እና ሶስት የጥይት መጋዘኖችን አጥታለች። * አዞቭ ሩሲያ ውስጥ የታገደ አሸባሪ ድርጅት ነው ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia