ምዕራባውያን ሀገራት በእስያ ፓስፊክ የላቁ የጦር መሳሪያዎችን በማሰማራት ውጥረት እንዲያይል አድርገዋል ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ተናገሩ የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ከደቡብ ምሥራቅ እስያ ሀገራት ማሕበር 'አዥያን' የመሪዎች ጉባኤ በኋላ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ያነሷቸው ሌሎች ቁልፍ ነጥቦች፡- ◾ የምዕራባውያን ሀገራት በእስያ ፓስፊክ አዲስ ወታደራዊ መሳሪያዎችን በማሰማራት በአካባቢው ያለውን ውጥረት እያባባሱ ነው። ◾ ሩሲያ የአሜሪካ እና ደቡብ ኮሪያ የጋራ የኒውክሌር እቅድ ተነሳሽነቶች ያሳስባታል። ◾ ሞስኮ አዥያን የአሜሪካ የረዥም ርቀት ሚሳኤሎች በእስያ ፓስፊክ መሰማራታቸው የሚፈጥረውን ተያይዥ ስጋቶች እንደሚረዳ ተስፋ ታደርጋለች። ◾ ዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ተቆጣጣሪ በአካባቢው ያለውን ሥልጣን ተጠቅሞ የኦኩስ ጥምረት ላይ ግፊት እንዲያሳድር ሩሲያ ታሳስባለች። ◾ የአዥያን ሀገራት ከምዕራቡ ዓለም ጋር መጋጨትን አይፈልጉም ነገር ግን በአካባቢው የኔቶን ተጽእኖ ይቃወማሉ። ◾ ሩሲያ እና የአዥያን ሀገራት አዲስ የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ አጋርነት እቅድ አዘጋጅተዋል። ◾ ዩክሬን ውስጥ ያለውን ግጭት ለመፍታት የሚቀርቡ የማያዋጡ ሀሳቦች ላይ አስተያየት መስጠት ምንም ፋይዳ የለውም፣ ሆኖም ሩሲያ አሁን ያለውን ሁኔታ ግንዛቤ ውስጥ የከተቱ እውነተኛ ሀሳቦች ላይ ለመወያየት ዝግጁ ነች። ◾ የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዋንግ ዪ ከዩክሬን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲሚትሮ ኩሌባ ጋር ስላደረጉት ውይይት ለላቭሮቭ አሳውቀዋል ሆኖም ቤጂንግ በዩክሬን ላይ ያላት አቋም አሁንም ተመሳሳይ ነው። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia