የሩዋንዳ ፕሬዝዳንት ፖል ካጋሜ 99.18% ድምጽ በማግኘት በድጋሚ ተመረጡ
ዘጠኝ ሚሊዮን ከሚጠጉ የተመዘገቡ መራጮች የተሳትፎ መጠን 98.20% እንደነበር የብሔራዊ ምርጫ ኮሚሽን አስታውቋል።
ሌሎቹ ሁለቱ እጩዎች የዴሞክራሲያዊ አረንጓዴ ፓርቲ ተወካይ ፍራንክ ሀቢኔዛ እና ገለልተኛው ፊሊፕ ምፓይማና እያንዳንዳቸው 0.5% እና 0.32% ድምጽ አግኝተዋል።
የመጨረሻው የምርጫ ውጤት ሐምሌ 20 ይፋ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
ባለፉት ሶስት ምርጫዎች ከ93% በላይ ድምጽ ያገኙት ካጋሜ የ1994ቱን የሩዋንዳ የዘር ማጥፋት ለማስቆም ባደረጉት ጥረት እና ሀገሪቱን ወደ ማራኪ የኢንቨስትመንት እና እርዳታ መዳረሻነት በመለወጣቸው በምእራባውያን እና በአህጉሪቱ መሪዎች ይመሰገናሉ።
ሆኖም በጎረቤት ሀገር ዲሞክራሲያዊ ኮንጎ ሪፐብሊክ የኤም 23 አማፂያንን ይደግፋሉ በሚል ውንጀላ ነቀፌታ የሚደርስባቸው ሲሆን ውንጀላውን በተደጋጋሚ አስተባብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia