በአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ እጩ ተወዳዳሪ ትራምፕ ላይ ስለተደረገው የግድያ ሙከራ እስካሁን የሚታወቁ ጉዳዮች
▪ ትራምፕ ከግድያ ሙከራው በኋላ በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙ የትራምፕ ረዳቶች ተናግረዋል።
▪ የህግ አስከባሪ ባለስልጣናት በትራምፕ የግድያ ሙከራ ዙሪያ ለባይደን ማብራሪያ ሰጥተዋል።
▪ ባይደን በፔንስልቬንያ በተደረገው የትራምፕ የድጋፍ ሰልፍ ወቅት የነበረውን የደህንነት እርምጃዎችን በሙሉ እንዲገመገም ትዕዛዝ ሰጥተዋል።
▪ የመገናኛ ብዙሃን ምንጮችን ጠቅሰው እንደተናገሩት የግድያ ሙከራ ያደረገው ግለሰብ ከአክራሪ ድርጅቶች አልያም "ትልቅ ሴራ" ስለመኖሩ የተገኘ ፍንጭ አለመኖሩን ገልጸዋል።
▪ ተኳሹ የተጠቀመበት ሽጉጥ አባቱ በህጋዊ መንገድ የገዛው እንደሆነ ተገልጿል።
▪ ተጠርጣሪው ቶማስ ማቲው ክሩክስ በትምህርት ቤት ውስጥ " ዝምተኛ ልጅ" እንደነበር እና ብዙ ጓደኞች ያልነበሩት እንደነበር ተገልጿል።
▪ የ20 አመቱ ተጠርጣሪ ወንጀለኛ ሪፐብሊካን እንደነበረ የፔንስልቬንያ የመራጮች መዛግብት አመላክቷል።
▪ በተጠርጣሪው ቤት እና መኪና ውስጥ ፈንጂ የሚሠሩ ቁሳቁሶች ተገኝተዋል።
▪ የአካባቢው ፖሊሶች እና የአይን እማኞች ከድጋፍ ሠልፉ በፊት ተኩስ የከፈተው ግለሰብ ላይ አጠራጣሪ ባህሪ ተመልክተው መረጃውን ለደህንነት አገልግሎት ሠራተኞች ሪፖርት አድርገው ነበር።
▪ የፔንስልቬንያ የድጋፍ ሰልፍ ታዳሚዎች የግድያ ሙከራው እንዲፈጸም የፈቀዱት የደህንነት አባላት ባሳዩት “የደህንነት ሥነ ምግባር መጣስ” አስደንግጧቸዋል።
▪ ተጠርጣሪው የተኮሰበት ጣሪያ የምርጫ ቅስቀሳ ዝግጅቱ ከመደረጉ ቀደም ብሎ ፍተሻ ተደርጎ እንደነበር ተገልጿል።
▪ የዩናይትድ ስቴትስ የተወካዮች ምክር ቤት የሪፐብሊካን አባል የሀገሪቱን የሀገር ውስጥ ደህንነት ኃላፊ የትራምፕን ደህንነት ለማስጠበቅ ፈቃደኛ አልሆነም ሲሉ ከሰዋል።
▪ የትራምፕ የደህንነት ጥበቃ እንዲጨምር የቀረበለት ጥያቄ መኖሩን የአሜሪካው ደህንነት አገልግሎት ውድቅ አድርጓል።
▪ የትራምፕ የምርጫ ቅስቀሳ ሰራተኞች እሁድ በዋሽንግተን ዲሲ እና ዌስት ፓልም ቢች ያሉ ቢሮዎችን እንዳይሄዱ ተነግሯቸዋል፤ ምክንያቱም የደህንነት ፍተሻዎች መደረግ ስላለበት እንደሆነ ተነግሯል።
▪ እ.አ.አ ከሐምሌ15-18 የሚካሄደው የሪፐብሊካን ብሔራዊ ኮንቬንሽን የጸጥታ እቅድ እየተከለሰ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia