የሩሲያ ጦር ኃይል ባለፉት 24 ሰዓታት ወደ 1,500 የሚጠጉ የዩክሬን ወታደሮችን መግደሉ የመከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የሚኒስቴሩ ልዩ ወታደራዊ ዘመቻን አስመልክቶ ያወጣው ተጨማሪ ሪፖርት:-
የደቡብ ተዋጊ ቡድን 15 ተሽከርካሪዎችን እና የስትሮላ-10 ሚሳይል ሲስተም ማጓጓዣ አስወንጫፊን አውድሟል።
ፖላንድ ሰራሹ 155-ሚሜ ክራብ ሃውትዘር፣ በርካታ አሜሪካ ሰራሹን155-ሚሜ ኤም 198 እና በዩኬ የተሰራ ኤፍኤች-70 ዋይትዘር እና ሌሎች የጦር መሳሪያዎች ወድመዋል።
የሰሜን ጦር ቡድን በካርኮቭ ክልል ስምንት የመልሶ ማጥቃት ሙከራዎችን አክሽፋል።
ጠላት አሜሪካ ሰራሽ 155 ሚሜ ኤም 77፣152-ሚሜ ዲ-20፣ 122-ሚሜ ዲ-30 ሃውትዘር፣100 ሚሜ ራፒራ ፀረ-ታንክ መሳሪያሽ ፤የፕላስተን ሲግናሎች የስለላ ጣቢያ እና ሁለት አንክላቭ የኤሌክትሮኒክስ ጦርነት ጣቢያዎችን አጥተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia