የሐምሌ 05 ምሽት ዋና ዋና የዓለም ዜናዎች፡-
🟠 በማዕከላዊ ናይጄሪያ ፕላቶ ክልል አርብ ዕለት አንድ ትምህርት ቤት ተከስክሶ 16 ተማሪዎች መሞታቸውን አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል። በደርዘን የሚቆጠሩ ፍርስራሽ ውስጥ ተቀብረው ሊገኙ እንደሚችሉ የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
🟠 የኬንያ ፖሊስ አዛዥ የተነሳውን ሀይለኛ ተቃውሞ ተከትሎ ስራቸውን ለቀዋል። ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ የጃፌት ኩሜን "የስራ መልቀቂያ እንደተቀበሉ" የፕሬዝዳንቱ ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
🟠 ፑቲን ኪዬቭ በዛፖሪዝሂያ የኑክሌር ማበልፀጊያ ጣቢያ ላይ ቀጥተኛ ጥቃት እያደረሰች እንደሆነ እና ጉዳዩ ልዩ ትኩረት እንደሚያስፈልገው ከዛፖሪዝሂያ ክልል ገዥ ጋር በተገናኙበት ወቅት ተናግረዋል።
🟠 ዩክሬን የኪዬቭ ሃይድሮ ኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ጣቢያን እና የኬኔቭ የውሃ ማጠራቀሚያ ግድብን ለማውደም በዝግጅት ላይ ነች ያሉት የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ይህ በሩሲያ ፌደሬሽን ላይ
ሌላ አላስፈላጊ ትንኮሳ ይሆናል ብለዋል።
🟠 አነጣጥሮ ተኳሽ የረዥም ርቀት የጦር መሳሪያዎችን በመጠቀም ዩክሬን በሚገኙ ወታደራዊ ኢላማዎች ላይ 39 ጥቃቶችን በአንድ ሳምንት ውስጥ እንዳካሄደ የሩሲያ ጦር ዘግቧል።
🟠 የወቅቱ የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሃንጋሪ ብትሆንም ጠቅላይ ሚኒስትር ቪክቶር ኦርባን በአዲሱ የአውሮፓ ፓርላማ የመጀመሪያ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ሳይጋበዙ ቀርተዋል።
🟠 የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ማክሮን ሐምሌ 9 የጠቅላይ ሚኒስትር ጋብርኤል አታታል እና የመንግሥታቸውን መልቀቂያ እንደሚቀበሉ ፍራንስ ኢንፎ ዘግቧል።
🟠 የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ባይደንን ከምርጫ ውድድር ለማስውጣት ሴራ እየተጠነሰሰ ነው ሲል አክሲዮስ ጽፏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia