24 ሀገራት ብሪክስን ለመቀላቀል እየተጠባበቁ እንደሆነ የሩሲያ የላይኛው ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አስታወቁ
የሩሲያ የላይኛው ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ቫለንቲና ማትቪዬንኮ ለሮሲያ 24 ቻናል እንደተናገሩት "24 ሀገራት የብሪክስ አባል ለመሆን እየተጠባበቁ ነው።"
የነጻ መንግሥታት ኮመንዌልዝ ሀገራት ወደፊት የብሪክስ አባል ሊሆኑ የሚችሉበትን እድልም ውድቅ አላደረጉም።
ብሪክስ ለአዳዲስ እጩ ሀገራት መስፈርቶችን ማዘጋጀት አለበት ያሉት አፈ ጉባኤው መመዘኛው በጥቅምት ወር በሩሲያ ካዛን በሚካሄደው የብሪክስ ጉባኤ ሊፀድቅ እንደሚችል አክለዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia