ዚምባብዌ እ.አ.አ በ2026 አጋማሽ ላይ በአሜሪካ ዶላር መገበያየት ሙሉ በሙሉ ታቆማለችል።
"በሁለት አመት ጊዜ ውስጥ - እንደውም ሁለት አመት በጣም ሩቅ ነው - 'ዚግ 'በሁሉም የሀገሪቱ ክፍል ተሰራጭቶ የመገበያያ ገንዘብ ይሆናል" ማለታቸውን የዚምባብዌ ፕሬዝዳንት ኢመርሰን ምናንጋግዋን ጠቅሶ አንድ የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።“እዚያ ደረጃ ላይ እንደርሳለን፤ዶላር ይዘህ ወደ ሱቆቹ ስትሄድ አንቀበልም የሚሉበት ጊዜ ይመጣል።
ባለፈው ሚያዝያ፣ የሀገሪቱ ሪዘርቭ ባንክ አዲስ ብሄራዊ መገበያያ ገንዘብ ይፋ ማድረጓ ይታወሳል።ገንዘቡም የዚምባብዌ ጎልድ (ወይም በአጭሩ ዚግ) ሲባል፤በ100 ቶን ወርቅ እና በ100 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ክምችት የተደገፈ ነው።
በ2019 የበጋ ወቅት የዚምባብዌ መንግስት በሃገሪቱ የአሜሪካ ዶላር ዝውውርን ከልክሎ የነበረ ቢሆንም፤ ይሁን እንጂ ከዘጠኝ ወራት በኋላ ይህ ክልከላ ማንስቱ ይታወሳል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia