ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን በ220 ኪሎ ሜትር አዲስ መንገድ ትስስራቸውን እና ኢኮኖሚያዊ ግኑኝነታቸውን ሊያሳድጉ ነው
የደቡብ ሱዳን የሽግግር ብሔራዊ የህግ ምክር ቤት የፕሮጀክቱን የፋይናንስ ስምምነት ማፅደቁን የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ አስታውቋል።
ኢትዮጵያ የግንባታውን ወጪ በብድር መልክ የምትሸፍን ሲሆን ጎረቤቷ በነዳጅ አቅርቦት ትከፍላለች።
ከደቡብ ሱዳን መሪ ሳልቫ ኪር የመጨረሻውን ፍቃድ የሚጠብቀው ይህ ፕሮጀክት የደቡብ ሱዳን ፓሎይች፣ ማይወት እና ፓጋክ አካባቢዎችን ከኢትዮጵያ ድንበር አካባቢዎች ጋር የሚያገናኝ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia