ደቡብ አፍሪካ የመድበለ ፓርቲ መንግስት መሰረተች

ደቡብ አፍሪካ የመድበለ ፓርቲ መንግስት መሰረተች የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግረስ (ኤ.ኤን.ሲ) ከ32ቱ የካቢኔ ቦታዎች 20ውን ይዞ እንደሚቀጥል እሁድ ምሽት አስታውቀዋል። ፖል ማሻቲል የደቡብ አፍሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው በድጋሚ ተሹመዋል። የገንዘብ ሚኒስትሩ ኢኖክ ጎዶንግዋናም በሐላፊነታቸው ቀጥለዋል። ሮናልድ ላሞላ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው የተሾሙ ሲሆን አንጂ ሞትሼክጋ የመከላከያ ሚኒስትርነቱን ተረክበዋል። የኤ.ኤን.ሲ የቀድሞ ዋና ተቀናቃኝ እና አሁን የጥምር መንግስቱ ትልቁ አጋር ዴሞክራቲክ አሊያንስ ስድስት ቦታዎችን አግኝቷል። በፓርላማ ውስጥ ጥቂት መቀመጫ ያላቸው ፓርቲዎች በተለይም የኢንካታ ፍሪደም ፓርቲ በአጠቃላይ ስድስት ቦታዎችን አግኝቷል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
Sputnik
ደቡብ አፍሪካ የመድበለ ፓርቲ መንግስት መሰረተች የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግረስ (ኤ.ኤን.ሲ) ከ32ቱ የካቢኔ ቦታዎች 20ውን ይዞ እንደሚቀጥል እሁድ ምሽት አስታውቀዋል። ፖል ማሻቲል የደቡብ አፍሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው በድጋሚ ተሹመዋል። የገንዘብ ሚኒስትሩ ኢኖክ ጎዶንግዋናም በሐላፊነታቸው ቀጥለዋል። ሮናልድ ላሞላ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው የተሾሙ ሲሆን አንጂ ሞትሼክጋ የመከላከያ ሚኒስትርነቱን ተረክበዋል። የኤ.ኤን.ሲ የቀድሞ ዋና ተቀናቃኝ እና አሁን የጥምር መንግስቱ ትልቁ አጋር ዴሞክራቲክ አሊያንስ ስድስት ቦታዎችን አግኝቷል። በፓርላማ ውስጥ ጥቂት መቀመጫ ያላቸው ፓርቲዎች በተለይም የኢንካታ ፍሪደም ፓርቲ በአጠቃላይ ስድስት ቦታዎችን አግኝቷል። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia