የኤም 23 አማፂ ቡድን በምስራቅ ዲሞክራቲክ ኮንጎ ሁለት አካባቢዎችን መያዙ ተነገረ።
“የማርች 23 ንቅናቄ” (M23) የተሰኘው የአማፂ ሃይሎች ቡድን በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ምሥራቃዊ ሪፐብሊክ ካንያባዮንጋ (ሰሜን ኪቩ ግዛት) ከተማ አቅራቢያ ሁለት አካባቢዎችን ከከባድ ውጊያ በኋላ በተሳካ ሁኔታ መያዙን የሀገር ውስጥ ሬዲዮ ዘግቧል።
እ.አ.አ ሰኔ 27 ቀን ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጦር ኃይሎች ጋር ባደረጉት ከባድ ጦርነት የሚሪኪ እና የኪማኪ መንደሮች በአማፂያኑ ቁጥጥር ሥራ ውለዋል።ግጭቱ የአካባቢው ማህበረሰብ በብዛትእንዲሰደድ አድርጓል።
አንድ ህጻን ጨምሮ አምስት ሰዎች መሞታቸውንና በርካቶች መቁሰላቸውን የወጡ ቅድመ ዘገባ አመልክተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia