በምእራብ ኬንያ በተነሳ ተቃውሞ ሰባት ሰዎች ቆስለው ሆስፒታል ገብተዋል።
ሁሉም ተጎጂዎች በሆማ ቤይ ከተማ በተተኮሰ ጥይት ሳቢያ መቁሰላቸውን ሲትዝን ዲጂታል ሚዲያ ዘግቧል።
የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሀን እንደዘገቡት ፖሊስ በናይሮቢ ሰልፈኞችን ለመበተን አስለቃሽ ጭስ እና የጎማ ጥይቶችን መጠቀሙን ዘግበዋል። ሪፖርቶች ቢያንስ 22 ሰዎች መሞታቸውን እና 12 የሚደርሱ ዜጎችመቁሰላቸውን ቢያመላክቱም፤ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ በበኩላቸው ስድስት ወጣቶችን መሞታቸውን አስታውቀዋል።
በተመሳሳይ ረቡዕ ሩቶ አወዛጋቢውን ረቂቅ ህግ ማንሳታቸውን እና ተከታታይ ማሻሻያዎችን እንደሚያደርጉ አስታውቀው፤ ከተቃውሞ ሰልፍ መሪዎች ጋር ውይይት ለማድረግም ቃል መግባታቸው ይታወሳል።
ዘ ሲቲዝን ዲጂታል ከዚህ ቀደም የሀገሪቱ ትልቁ ጦር ወደ ፕሬዝዳንቱ መኖሪያ ቤት የሚወስዱትን መንገዶች ሁሉ እንደዘጉ እና ሁሉም መኪኖች ተለዋጭ መንገዶች እንዲጠቀሙ የተዘዋወሩ እያደረጉ ነው። ወታደራዊ መሣሪያዎች በፕሬዚዳንቱ መኖሪያ አቅራቢያ መደርደራቸውን እና መንገዶች ሁሉ መዘጋታቸው ዘግቦ ነበር።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia