የሰኔ19 ማለዳ ዋና ዋና የአለም ክስተቶች፡-
🟠 የኬንያ ፕሬዝዳንት ተቃውሞው ለብሔራዊ ደኅንነት ስጋት እና በሕገ መንግስታዊ ስርዓቱ ላይ የተሰነዘር ጥቃት ነው በማለት ሰራዊቱን ስርዓት እንዲያስመልስ አሰማሩ፣
🟠 በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የተመድ ልዑክ በደቡብ ኪቩ ግዛት የሚገኘውን ዋና ቢሮውን በኪንሻሳ ጥያቄ መሰረት ዘግቷል፣
🟠 ደቡብ አፍሪካ የዝንጀሮ ፈንጣጣ ቫይረስ በሽታ ሶስተኛ ሞት ያስመዘገበች ሲሆን በአጠቃላይ 16 ሰዎች በበሽታው እንደተያዙ ተረጋግጧል፣
🟠 የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት በሀገሪቱ የተከሰተውን የኮሌራ ወረርሽኝ ተከትሎ በብሔራዊ የበሽታ መቆጣጠሪያ ማዕከል የተቋቋሙ የአደጋ ጊዜ ምላሽ ማዕከላትን የሚቆጣጠር የካቢኔ ኮሚቴ እንዲቋቋም አዘዙ፣
🟠 በአሜሪካ አነሳሽነት በሩሲያ የመከላከያ ሚኒስትር እና የፔንታጎን ኃላፊ መካከል የስልክ ውይይት ተደረገ። ሩሲያ ለዩክሬን መከላከያ ኃይል የሚቀርቡ የአሜሪካ ጦር መሳርያዎች ግጭቱን የማባባስ ስጋት እንዳላቸው ለአሜሪካ ተናግራለች፣
🟠 ጁሊያን አሳንጅ ከአሜሪካ ጋር ባደረገው ስምምነት መሰረት ጥፋተኝነቱን ተቀብሎ ነፃነቱን ካገኘ በኋላ ከፍርድ ቤት በጩኸትና ጭብጨባ ታጅቦ ወጥቷል፣
🟠 ሰሜን ኮሪያ የባላስቲክ ሚሳኤል ማስወንጨፏን የደቡብ ኮሪያ መገናኛ ብዙሃን ዘገቡ
🟠 የሩሲያ ፌዴራል የሕክምና-ባዮሎጂ ኤጀንሲ የዩክሬን ጦር ኃይሎች በዛፖርዥያ የጨረር መቆጣጠሪያ ጣቢያ ያደረሱትን ውድመት እየተከታተልኩ ነው አለ፣
🟠 የሩሲያ ፓስፊክ መርከቦች የባስቴዮን የባህር ዳርቻ ሚሳኤል ስርዓቶች የጠላት መርከቦችን የመምታት ልምምድ አካሄዱ፣
🟠 አወራራጆች በትራምፕ እና ባይደን ክርክር ወቅት ማን ቀድሞ ይሳደባል የሚል ውርርድ እየተቀበሉ እንደሆነ ተዘገበ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia