በደቡብ አፍሪካ የተካሄደው አጠቃላይ የምርጫ ውጤት በምንም መልኩ ከሩሲያ ጋር ያለውን ግንኙነት እንደማይጎዳ እና ወዳጃዊ በሆነ መንገድ መጎለበቱን እንደሚቀጥል የሀገሪቱ አምባሳደር ገለፁ
"ሀገራቱ ግንኙነታቸውን ወዳጃዊ በሆነ መንገድ ያዳብራሉ። የምርጫውን ውጤት ተከትሎ አዲስ መንግስት የማቋቋም ሂደቶችን ገና አላጠናቀቅንም። ነገር ግን የግንኙነታችን መሰረት ባለበት እንደሚቀጥል እርግጠኛ ነኝ። በደቡብ አፍሪካ ሩሲያን የተመለቱ ቁልፍ የውጭ ፖሊሲ አቅጣጫዎች ባሉበት ይቀጥላሉ፡ የጠለቀ ታሪካዊ መሰረት አላቸው" ሲሉ በሩሲያ የደቡብ አፍሪካ አምባሳደር ምዙቩኪሌ ጄፍ ማኬቱካ ለሩሲያ መገናኛ ብዙሃን ተናግረዋል።
በየካቲት ወር አምባሳደሩ ደቡብ አፍሪካ ከፕሬዝዳንታዊ ምርጫው በኋላ ተቃዋሚዎች ወደ ስልጣን የሚመጡ ከሆነ የውጭ ፖሊሲ አቅጣጫዋን ልትቀይርና ከብሪክስ ልትወጣ እንደምትችል ተናግረው ነበር። ሆኖም ግንቦት 21 የተካሄደውን አጠቃላይ ምርጫ ተከትሎ ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ ሰኔ 7 በድጋሚ መሪ ሆነው ተመርጠዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia