ሰርጌ ላቭሮቭ ከኮንጎ ሪፐብሊክ አቻቸው ዣን ክላውድ ጋኮሶ ጋር መወያየታቸው ተገለፀ
ሁለቱ ዲፕሎማቶች በሩሲያ እና ኮንጎ መካከል ያለውን "የተለመደ ወዳጃዊ" ግንኙነት ለማጠናከር በሚከተሉት ግቦች ላይ ውይይት አድርገዋል፦
በንግድ፣ ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት ዘርፎች የጋራ ተጠቃሚነት ያለው አጋርነት መፍጠር፣
በኢነርጂ ዘርፍ የጋራ ፕሮጀክቶችን መተግበር፣
በኮንጎ ሪፐብሊክ የማዕድን ክምችቶችን ማበልፀግ።
ሚኒስትሮቹ ሞስኮ እና ብራዛቪል ፖለቲካዊ ምክክራቸውን ለማጠንከር እና ሁለቱ ሀገራት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና በሌሎች የባለብዙ ወገን መድረኮች የተቀናጀ አቀራረብ ለመፍጠር ቁርጠኛ እንደሆኑ አፅንኦት ስጥተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia