በሩሲያ ዳግስታን ውስጥ የተፈፀመው ሽብር ጥቃት የቅርብ ጊዜ ዜናዎች፡-
▪ እንደ የስፑትኒክ ምንጭ ገለፃ ስድስት ታጣቂዎች ተወግደዋል፣
▪ በጥቃቱ ከ15 በላይ ፖሊሶች እና በርካታ ሰላማዊ ሰዎች ተገድለዋል፣
▪ የጸጥታ ሃይሎች ጥቃቱ በተፈፀመበት ቦታ ምርመራ እያካሄዱ ሲሆን ትናንሽ መሳሪያዎችና ጥይቶችን ማግኘታቸውን የብሔራዊ ፀረ-ሽብር ኮሚቴ ገልጿል፣
▪የሽፍታዎቹን ተባባሪዎች የማፈላለግ ስራ በክልሉ ቀጥሏል፣
▪ በዳግስታን ከሰኔ 17-19 የሶስት ቀን ሀዘን ታውጇል፣
▪ የክልሉ ገዥ ሜሊኮቭ አሸባሪዎቹ "ከውጭ" ስልጠና የወሰዱ ናቸው ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል፣
▪ ለሟች እና ጉዳት ለደረሰባቸው ቤተሰቦች የቁሳቁስ ድጋፍ ይደረግላቸዋል፣
▪ የኡዝቤኪስታን፣ የኪርጊስታን እና የካዛኪስታን መሪዎች ሀዘናቸውን ገልጸው ጥቃቱን አውግዘዋል፡፡
ተንቀሳቃሽ ምስሉ:- በብሔራዊ ፀረ-ሽብር ኮሚቴ የተለቀቀ የፀረ-ሽብር ኦፕሬሽን፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia