#አጫጭርዜና
የስፑትኒክ ኢትዮጵያ ትኩስ ዜናዎችን ይከታተሉ፦
🟠 የክራይሚያ ልሳነ ምድር ትልቋ ከተማ በሆነችው ሴቫስቶፖል በደረሰው የዩክሬን ሚሳኤል ጥቃት የሟቾች ቁጥር አምስት መድረሱን ገዥው ሚካሂል ራዝቮዛይቭ ገለፁ።
🟠 በሴቫስቶፖል ሰላማዊ ዜጎች ላይ ለደረሰው የታቀደ የሚሳኤል ጥቃት ተጠያቂነት በዋነኝነት መሳሪያዎቹን ባቀረበችው ዋሽንግተን እንዲሁም የጥቃቱ መነሻ በሆነው የኪዬቭ አገዛዝ ላይ እንደሚያርፍ የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ገልጿል።
🟠 የታላቁ የአርበኞች ጦርነት ትልቁ እና ስኬታማ ስትራቴጂክ ዘመቻ የባግሬሽን ጥቃት ከ80 ዓመት በፊት በዛሬ ቀን ነው የተጀመረው።
🟠 ሩዋንዳ በሚቀጥለው ወር ለሚካሄደው ፕሬዝዳንታዊ እና የፓርላማ ምርጫ ቅስቀሳ ጀምራለች።
🟠 በዶንባስ ውስጥ የሚያገለግል ፈረንሳዊው የምዕራባዊ እና የሩሲያ ወታደራዊ መሳሪያዎችን አወዳድሯል።
🟠 የማሊ የሽግግር ፕሬዝዳንት አሲሚ ጎይታ ፈረንሳይ
የማሊን ኢኮኖሚ ለመጉዳት ሀሰተኛ ሴኤፍኤ ፍራንክ ኖቶችን ታትማለች ሲሉ ከሰሱ።
🟠 10 የፖለቲካ ፓርቲዎች የደቡብ አፍሪካ ጥምር መንግስትን ሊቀላቀሉ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia