ኪዬቭ በሴቫስቶፖል በፈጸመችው ጥቃት የተገደሉት ሰዎች ቁጥር 3 ህጻናትን ጨምሮ 5 እንደደረሰ የአካባቢው አስተዳዳሪ አስታወቁ
ፕሬዝደንት ቭላዲሚር ፑቲን በሴቫስቶፖል ባህር ዳርቻ ለተገደሉ ሰዎች ቤተሰቦች ሀዘናቸውን መግለፃቸውን የከተማው አስተዳዳሪ ገልጸዋል።
ፑቲን ሴቫስቶፖል ውስጥ ከደረሰው ጥቃት በኋላ ከሩሲያ መንግስት የማህበራዊ ዘርፍ እና የጤና አአገልግሎት አመራሮች ጋር ግንኙነት እያደረጉ መሆናቸውን የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ለስፑትኒክ ተናግረዋል። እንደ ቃል አቀባዩ ገለጻ ፕሬዝደንቱ ከሀገሪቱ ጦር ጋር በተደጋጋሚ እየተገናኙ ነው።
የሀገሪቱ መሪ የፕሬስ ፀሐፊ አሁን ዋናው ነገር ለተጎጂዎች አስፈላጊውን እርዳታ መስጠት ነው ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia