ልዩ ቃለመጠይቅ| የኢትዮጵያ መንግሥት የቱሪዝም ዘርፍ ለኢኮኖሚው የሚያበረክተው አስተዋፅኦ አሁን ካለው 7.

ልዩ ቃለመጠይቅ| የኢትዮጵያ መንግሥት የቱሪዝም ዘርፍ ለኢኮኖሚው የሚያበረክተው አስተዋፅኦ አሁን ካለው 7.4% "ከፍተኛ ጭማሬ" ያሳያል ብሎ እንደሚጠብቀ የሀገሪቱ የቱሪዝም ሚኒስትር ገለፁ “በዚህ ዓመት የታየው የቱሪስቶች ቁጥር ከወረርሽኙ በፊት በ2019 ከነበረው ሲነፃፀር ብልጫ አለው" ሲሉ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ሚኒስትር ናሲሴ ቻሊ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ ቱሪዝምን ለማሳደግ መንግሥት ከወሰዳቸው እርምጃዎች መካከል የቱሪዝም ሚኒስቴርን ራሱን የቻለ ሚኒስቴር አድርጎ ማቋቋም እና ዘርፉ ላይ ከፍተኛ ወጪ ማድረግ እንደሚጠቀስ አንስተዋል። "ባለፉት 2-3 ዓመታት በቱሪዝም መሠረተ ልማት ላይ ያለማቋረጥ የመዋዕለ ነዋይ ፈሰስ ስናደርግ ቆይተናል በተለይም ለአዲስ መዳረሻዎች አዳዲስ መንገዶችን፣ አዲስ የአውሮፕላን መንገዶች፣ አዲስ የአየር ማረፊያዎች እና ሌሎች መሰረታዊ የቱሪስት መሠረተ ልማቶችን በመጨመር ላይ እንገኛላን" ሲሉ ሚኒስትሯ ጠቁመዋል። ሌላው "ተጓዦች ወደ ኢትዮጵያ መጥተው እንዲጎበኙ ቀላል የሚያደርገው" እርምጃ "ከ190 በላይ ለሚሆኑ ሀገራት ኢ-ቪዛ ወይም የመዳረሻ ቪዛ አገልግሎት" መስጠት የሚያስችለው የቪዛ ማሻሻያ ነው። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia
Sputnik
ልዩ ቃለመጠይቅ| የኢትዮጵያ መንግሥት የቱሪዝም ዘርፍ ለኢኮኖሚው የሚያበረክተው አስተዋፅኦ አሁን ካለው 7.4% "ከፍተኛ ጭማሬ" ያሳያል ብሎ እንደሚጠብቀ የሀገሪቱ የቱሪዝም ሚኒስትር ገለፁ “በዚህ ዓመት የታየው የቱሪስቶች ቁጥር ከወረርሽኙ በፊት በ2019 ከነበረው ሲነፃፀር ብልጫ አለው" ሲሉ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ሚኒስትር ናሲሴ ቻሊ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ ቱሪዝምን ለማሳደግ መንግሥት ከወሰዳቸው እርምጃዎች መካከል የቱሪዝም ሚኒስቴርን ራሱን የቻለ ሚኒስቴር አድርጎ ማቋቋም እና ዘርፉ ላይ ከፍተኛ ወጪ ማድረግ እንደሚጠቀስ አንስተዋል። "ባለፉት 2-3 ዓመታት በቱሪዝም መሠረተ ልማት ላይ ያለማቋረጥ የመዋዕለ ነዋይ ፈሰስ ስናደርግ ቆይተናል በተለይም ለአዲስ መዳረሻዎች አዳዲስ መንገዶችን፣ አዲስ የአውሮፕላን መንገዶች፣ አዲስ የአየር ማረፊያዎች እና ሌሎች መሰረታዊ የቱሪስት መሠረተ ልማቶችን በመጨመር ላይ እንገኛላን" ሲሉ ሚኒስትሯ ጠቁመዋል። ሌላው "ተጓዦች ወደ ኢትዮጵያ መጥተው እንዲጎበኙ ቀላል የሚያደርገው" እርምጃ "ከ190 በላይ ለሚሆኑ ሀገራት ኢ-ቪዛ ወይም የመዳረሻ ቪዛ አገልግሎት" መስጠት የሚያስችለው የቪዛ ማሻሻያ ነው። ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia