አልጄሪያ እና ቱኒዚያ የሩሲያን ገብስ በከፍተኛ ደረጃ ወደ ሀገር ውስጥ ከሚያስገቡ ቀዳሚ 5 ሀገራት መካከል ሆኑ
ቱኒዚያ እና አልጄሪያ 266 ሺህ ቶን እና 182 ሺህ ቶን እንደ ቅደም ተከተላቸው የሩሲያን ገብስ በከፍተኛ ደረጃ ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት ከመጀመሪያዎቹ ቀዳሚ 5 ሀገራት መካከል መግባታቸው ከጥር እስከ ግንቦት 2024 ያለው የፌዴራል ማዕከል አግሮ ኤክስፖርት (Agroexport) ሪፖርት ያሳያል።
እ.አ.አ በ 2023/2024 መጨረሻ ሩሲያ 8.8 ሚሊዮን ቶን የገብስ ምርት ወደ ውጭ ሀገር እንደምትልክ ተገምቷል፤ ባለፈው የምርት ዘመን ወደ ውጪ የተላከው 5.64 ሚሊዮን ቶን ነበር።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ @sputnik_ethiopia